ከዛሬ አምስት ዓመት በፊት አገራችን ኢትዮጵያ ፈውስ ያስፈልጋታል በሚል አንድ ጽሑፍ አዘጋጅቼ በማኅብራዊ ገጽ ላይ መለጠፌ ይታወቃል። የጽሑፌ ርዕስ “ምድራችሁን እፈውሳለሁ ይላል እግዚአብሔር” የሚል ሲሆን ብዙዎች አንብበውታል። የጽሁፉ ቁልፍ አሳብ ምድራችን/ አገራችን/ ኢትዮጵያ ያጣችሁ በረከት ሳይሆን ፈውስ ስለሆነ ለፈውሷ እንጸልይ የሚል ነበር። ምድራችን መታመሟን ሁሉም ያውቀዋል። እግዚአብሔር አምላከ “ምድራችሁን እፈውሳለሁ” ያለው ምድር በሕመም ስለምትሰቃይ ነው። የአገራችን ሕመም ቀስ በቀስ የውስጥ ሰውነትን እያዳከሙ በጊዜ ቆየታ ሕይወት እንደሚቀጥፉ ሥር የሰደዱ ሕመሞች ነው። እነዚህ chronic በመባል የሚታወቁ ሲሆን ይኸውም በሰውነት ውስጥ ሥፍራ ይዞ ቀስበቀስ አካልን የሚያደክም አደገኛ የሕመም እድገት ነው። ሰውን የሚገድሉ ሥር የሰደዱ ሕመሞች ናቸው።
እንደዚሁም ሁሉ ምድርም ለሕይወት በሚያሰጋ በከባድ በሽታ ትታመማለች። ስለዚህም ነው እግዚአብሔር ምድራችሁን እፈውሳለሁ ያለው። ሰው ሲታመም ወደ ሐኪም ቤት ይወሰዳል። ምድር ስትታመም ግን ከመለኮት ጣልቃ ገብነት በቀር ሌላ ሐኪም ቤት የለም። ምድር ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ምን ሐኪም የላትም። መድሃኒቱም ያለው በእርሱ እጅ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ መታመሟን ያወቅነውም ብዙ ቆይተን አሁን በቅርቡ ቢሆንም እኛም አብረን እየታመምን ነው። ስለዚህ ይህቺን አገር የሚወዳት ሁሉ ሊጸልይላት ይገባዋል። የአገሬ ፍቅር አለኝ የሚል ማንም ከሚዘፍንላት ይልቅ ፣ ከሚዘምርላትም ይልቅ ፣ አሁን የሌላትን መንፈሳዊ ስም ከሚስጣት ይልቅ ሊጸልይላት ይገባዋል። ስለዚህች አገር ማቅ ለብሰን ፣ አመድም ነስንሰን ፣ ከካህን እስከ ምዕመን ቢቻል በር ዘግተን ፣ ከእህል ከውሃ ተለይተን ማልቀስና መቃተት ያለብን ጊዜ ቢኖር አሁን ነው። ሕመሞቿን በቀላል አማርኛ ፣ እንደሚከተለው እንድገልጽ ይፈቀድልኝ።
፩. በዘርና በጐሳ የሚከፋፍል ሕመም።
እስትሮክ አንዱን የአካል ክፍል ለይቶ የሚጐዳ የህመም ዓይነት ነው። ይህ ቀኙ እየሠራ ግራውን እንዳይንቀሳቀስ የሚያደርግ ወይም ግራው ደህና ሳለ የቀኙን በኩል ከላይ እስከታች የሚያሽመደምድ በሁሉ የተረገመ በሽታ ነው። ። ይህ ዓይነቱ በሸታ ቶሎ ባይገድልም የሕመምተኛውን የመዳን ተስፋ ያጨልማል። እንደዚሁም የአገራችን ሕመም በዘር በጐሳ፣ በወገን፣ በክልል የሚከፋፈል እንደ ስትሮክ ዓይነት ነው። ሌሎች የበለጠጉና ያደጉ አገሮች የጐሳ ፖለቲካን /Ethnic politics/ በጐጂነቱ ፈርጀው ወደ እንጥሮጦስ ከጣሉና ዳግም ተንስቶ ለአገራቸውና ለሕዝባቸው ጥፋት እንዳያመጣ መንገዱን በጥርብ ድንጋይ ከዘጉ በኋላ ይህ አደገኛ ፖለቲካ በአገራችን የዕድገት፣ የዴሞክራሲና የልማት አምድና ምሶሶ ተደርጐ ተወስዷል። ኢትዮጵያ የብዙ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የቋንቋዎች፣ የባህሎች ፣ የዘርፈ ብዙ ማህበራዊ እሴቶች ባለቤት መሆኗ ከፍሎ ለሚያሰቃይ በሽታ ምቹ አድርጐአታል። የአገራችን ሕዝቦች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት እንደጌጥ እየቆጠሩ እርስ በእርሳቸውም እየተቻቻሉ ፣ በአካባቢቸውም ያለውን ግብአት በጋራ እየተጠቀሙ ያለ አንዳች መገፋፋት ለዘመናት መኖራቸው፤ ሰሜኑ ከደቡቡ ሕዝብ፣ ምሥራቁ ከምዕራቡ፣ የመሀሉ ከዳሩ ሕዝብ ጋር ተረዳድተውና ተከባብረው የኖሩባትና የሚኖሩባት አገር መሆኗ እውን ቢሆንም አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ባመጣብን ከፋፋይ ፖለቲካ የተነሳ ሕዝቦቿ እርስ በርሳቸው ከመከፋፈልም አልፎ እስከ መገዳደል ደርሰዋል። ሥር የሰደደ በሽታ የሰውን የቀድሞ መልኩን እንደሚለውጠው ሁሉ አሁን ያለችው ኢትዮጵያ ድሮ የምትታወቀዋ በታሪክ ስለ እርሷ የምንሰማው፣ምሁራን ያስቀሩልንን ታሪክ የምናነበው ሳይሆን ታሪኳ ተቀይሮ፣ መልኩዋም ጠፍቶ ፣ ከቀደሞው ታሪክ ጋር የማይገጥም እንግዳ ነገር እንድናይ የሚያደርግ ሕመም ሥር እየሰደደባት ነው።
በአገሪቱ ያለው እያንዳንዱ ብሔር መነሻ ማንነት ቢኖረውም በቅድሚያ ሰው መሆኑን ያምናል፣ከዚያም ኢትዮጵያዊ መሆኑን ያምናል። አማራው አማራ ነኝ ቢልም ኢትዮጵያዊነቱን አይክድም ነበር። የበላይ ዘለቀ ልጅ ጐጃሜ ነኝ፣ ደግሞም ምንጃሬ፣ ሸንኮራ ነኝ ዘራፍ፣ዘራፍ ዘራፍ ቢልም ኢትዮጵያዊነቱን ሳይክድና ሳይለቅ ከሌላው ሕዝብ ጋር እርሱም አብሮ ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ያምን ነበር። ሌላው ብሔር ቢሆንም እንደዚያው ነው። የአባጁራፍ ልጅ ኦሮሞ ነኝ ፣ የካዎ ጦና ልጅ ወላይታ ነኝ፣ የንጉሥ አይማሎ ልጅ ጋሞ ነኝ፣ የንግሥት ፉራ ልጅ ሲዳማ ነኝ ወዘተ ቢልም ከሌሎች ሕዝቦች ጋር ኢትዮጵያዊ ነኝ፣ አገሪቱ የጋራችን ነች፣ ወንዙ ሸንተረሩ ተራራው፣ ጋራው፣ ሁሉ የጋራችን ነው፣ እያለ በልዩነቱ ውስጥ ያለውን ውበትና ጣዕም እያጣጣመና እያደነቀ፣ አንዱ የሌላውን ሕመም እየታመመ፣ በደስታውም አብሮ እየተደሰተ፣ ኢትዮጵያን በጋራ ተሸክሞ የኢህአዴግ መንግሥት አገሪቱን እስከሚቆጣጠርበት ጊዜ አደረሳት። ያውም ክብሯ ዝቅ ሳይል፣ ዳር ድንበሯ ሳይደፈር፣ አንድ ስንዝር መሬት ለጐረቤት አገር በድርድርም ሆነ ጦርን በመፍራት አሳለፎ ሳይሰጥ ነው ታዲያ! የኢህአዴግ መንግሥት ምድሩን ማስተዳደር ሲጀምር አፉን የፈታው “መገንጠል” ፣ “ክልል”፣ “የራስን መብት በራስ መወስን” በሚሉ ቃላቶች ነው። ቃላቶቹ/ አሳቦቹ ልበላቸው/ ለኢትዮጰያ ሕዝቦች አንድነትና እኩልነት ፣ ለመብታቸውም መከበር ዘብ የሚቆሙ ቢመስሉም አሁን ለሚታየው መከፋፈልና መናቆር የተጣሉ የመሠረት ድንጋዮች ናቸው። ቃላቶቹ አሳችና ግራ አጋቢዎች ናቸው። አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት የሕዝቦችን ትሥሥር ለመበጣጠስ የቻለው በእነዚህ የመሠረት ድንጋዮች ላይ ቆሞ ነው። ይህ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ አንዱን ብሔር ከሌላው፣ አንዱን ክልል ከአንዱ ጋር የሚያባላው እነዚህን በሽታ አምጪ ሕዋስ የሆኑ ቃላቶችን በምድሪቱ ላይ በመበተን ነው። ይህም በመሆኑ ኢትዮጵያ ከተፈጠረችበት ጊዜ አንስቶ እስከአሁን ድረስ ተቻችለው የኖሩ፣ ተሳስበው፣ ተከባብረው፣ ተጋብተውና ተዋልደው ፣ በሁሉም ማኅበራዊ ጉዳዮች አንድ ሆነው በመልካም ትሥሥር ለዘመናት የቆዩ ሕዝቦች እርስ በርሳቸው ለመጐሻሸም፣ ለመገዳደል ፣ ለመፈነቃቀልና ለማሳደድና ለመሰደድ ከተጋለጡ ይኸው የአንድ ጎልማሳ ዕድሜ እያስቆጠሩ ነው። ለዚህ ሕመሟ መድኃኒት ያልተገኘላት አገራችን ሕመሟ እየጠናባት በመሆኑ መድኃኒትና መላ ፣ መፍትሔም ያስፈልጋታል። ከመጀመሪያውም መፍትሔ ሊገኝ በማይችል ሁኔታ መርዙ ስለተቀነባበረና በየቦታውም ስለተቀበረ ሕመሟ እየባሰባት መጣ። የኢሀአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝቦች በአንድነት እንዳይኖሩ በቋንቋና በብሔር እንዲከፋፈሉ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የሳለው የአገሪቱ ካርታና ክልላዊ መዋቅሩ እንኳ ቢታይ ብሔርን ባህልንና ቋንቋን መሠረት ያደረገ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ወደፊት አንዱ ከሌላው ለመገንጠል እንዲያመቸው ሆን ተብሎ የተሠራ ተንኮል መሆኑ ሳይገባን ኖረናል። በአሁኑ ጊዜ መቻቻልን ትተው ወንድም ወንድሙን በጦር እያሳደደ፣ ክልሌ ስለሆነ በዚህ አካባቢ መኖር ፣ መንቀሳቀስ ፣ መሥራት ወዘተ አትችልም እያለ አብሮት የኖረውን፣ አብሮት ያደገውን ያሳድደዋል። ሁለት ሰዎች ቢጣሉና አንደኛው ቢጐዳ እነማን ናቸው የተጣሉት ተብለው በሰውነታቸውና በስማቸው መሠረት መጠየቅና ማስረዳት አግባብ ሆኖ ሳለ አሁን የሚጠይቀው ብሔር ፣ ዘር ወይም ክልል ነው። ይቀጥልና የዚህ ብሔር የዚኛውን ብሔር ደበደበ፣ ወይም የዚህ ብሔር የዚኛውን ብሔር ገደለ ይባልና ጠቡ የብሔር ይሆናል። አሁንም ይቀጥልና ይህ ብሔር ከዚኛው ብሔር ጋር ተጣላ፣ ከዚሀ ብሔር ይህን ያህል ሰው ሞተ፣ ይህን ያህል ሰው ተጐዳ የሚል ዜና ይሰራጫል። ወያኔ ሕዝባችንን እጁን ይዞ ሀ ሁ ሂ እያለ ፊደል ያስቆጠረውና ያለማመደው ይህንን ክፉ ሥራ ነው። የግለሰቦቹ ጠብ ዕለታዊ ጉዳይ የግል እንጂ የብሔር ጠብ አልነበረም ግን የተዘረጋው መዋቅር እና የተቀመመው የፖለቲካ መርዝ ይህንን መሰል በሽታ በሕዝባችን ላይ አመጣ። እውነት ለመናገር አንዱ ሕዝብ አብሮት ከኖረው፣ በባህል ፣ በሃይማኖት በጋብቻ ወዘተ ተሳስሮ፣ ተቀላቅሎ፣ አንዱ ከሌላው ጋር ተጋብቶና ተዋልዶ ለዘመናት ከኖረበት ከሌላው ህዝብ ጋር መጋጨትም ሆነ መቃቃር እንደሚገባው የሚያምን ኢትዮጵያዊ የለም። የአማራ ሕዝብ ከሮሞና ከሌላው የሲዳማ ሕዝብ ከወላይታ ህዝብ ጋር ፣ ጉጂ ከቡርጂ ጋር መተላለቅ አይገባውም ነበር። በቅርቡ እንኳ በዝዋይ ከተማ በሁለት ኢትዮጵያውያን መካከል ጠብ ቢፈጥር የኦሮሞና የወላይታ ሕዝቦች ግጭት ተደርጐ መወሰዱ ፣ አሁን ደግሞ በምሥራቁ የአገራችን ከፍል የብዙዎችን ሕይወት እየቀጠፈ ያለው ቀውስ እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ የሚችል ነው። ሕመሙ በኢትዮጵያ መላ ሰውነቷ ላይ ስለተሠራጨ ይህ አሳዛኝ ነገር ሊሆን ቻለ። የኢህአዴግ ወያኔ መንግሥት መሪዎች አሸናፊውን ለመለየት በመሀል እንዳለ ታዛቢ ነገሩን በትዝብት ያዩታል ወይም እንደ ተመልካች ይዝናኑበታል እንጂ መፍትሔ አይሰጡበትም፤ የጸጥታ ሃይሉም ሬሳ ቆጥሮ ሪፖርት ያደርጋል እንጂ በሚተላለቀው ሕዝብ መካከል ገብቶ የሕዝቡን ዋስትና አያረጋግጥም፣ ምክንያቱም ፖሊቲካው ሲጠነሰስ የተፈለገው ይኸው ነውና። ይህ በሽታ ኢትዮጵያን እንዳያጠፋት የተቻለውን መፍትሔ ሁሉ መፈለግ ያሻል። ከመፍትሔዎቹ አንዱና ቀዳሚው በእግዚአብሔር ፊት ማልቀስ ነው። ያለዚያ አሁን የተበተነው ሕመም አመንጪ የፖለቲካ ሕዋስ አካሉዋን በጣጥሶና ገነጣጥሎ ይጨርሰዋል። መንግሥት እንደሆነ የኢትዮጵያን መሬት ሲያሻው ለጐረቤት አገር እየሸጠ ፣ ሲያስፈልገው ከመሃሉ አርሶ አደሩን አፈናቅሎ መሬቱን ለባዕድ እየሸጠ ሕዝባችን ላይ ድራማ ይሠራበታል፣ ቁማርም ይጫወትበታል። በምዕራቡ በኩል አንድ የአካል ክፍል ተቆርሶ ወደ ሱዳን በኩል ወድቋል። የነገ ተረኛ ማን እንደሆነ አናውቅም።
አካልን የሚደመስሰው የፖለቲካ ሕዋስ በቤተመንግሥት ብቻ ሳይወሰን ወደ ሃይማኖቱ ውስጥም መግባቱ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕጣ፣ በሕይወትም የመቆየቷን ጉዳይ የበለጠ አሳሳቢ አድርጐታል። ቸር ወሬ ያሰማን እንጂ ቤተክርስቲያንም በዘር ፣ በጐሳ ከተከፋፈለች ጊዜ የለውም። እንዲያውም ፈጥና ራሷን የሰባበረችው ቤተ ክርስቲያን ነች። በብሔር ወገንተኝነት ላይ የተመሠረተ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ አለ። መንግሥትም ለመከፋፈል ዓላማው እንዲያመቸው በሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የራሱ ካድሬዎች ሰግስጓል። በየእምነት ተቋማት ውስጥ የኢህአዴግ የደህንነት ካድሬዎች አሉ። የፖለቲካ መዋቅሩ ከመንግሥት ተቋማት እስከ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ድረስ ተዘርግቷል። የወንጌል ቃል በሚገለጥበት ሥፍራ ላይ ቆመው መንግሥትን የማሞካሸት የሚቃጣቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች ጥቂት አይደሉም።
የሕመም አምጪው ሕዋስ በአገር ቤት ብቻ ሳይወሰን ባህር ተሻግሮ በመምጣት ሕዝቦቿን እያተራመሳቸው ነው። ከቤተሰቦቻቸው ጋር በልጅነታቸው ከአገር የወጡ ልጆች የመጡበትን አገር ሲናገሩ ከምሥራቅ አፍሪካ ፣ ከኦሮሚያ ነው የመጣነው ሲሉ ከኢትዮጵያ ናችሁ ሲባሉ አይደለም ከኦሮሚያ ነው ይላሉ። እንግዲህ እነዚህ ልጆች ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንዳለች አያውቁም ማለት ነው። ከእነርሱ በኋላ የሚመጣው ትውልድ ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንደነበረች አድርገው እንደ ታሪክ መናገራቸው አይቀርም። ጂቡቲ ከኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገራት አንዷ እንደነበረች የማያውቅ ወጣት ብዙ እንደነበረ ሁሉ ኦሮሚያ ፣ አማራ፣ ሐሬሪ፣ ቤንሻንጉል ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ ወዘተ የሚባሉት አገሮች እንደ አንድ አገር በአንድ መንግሥት አስተዳደር ሥር ነበሩ እያሉ ማውራታቸው አይቀሬ ነው። ይህ የዘመኑ መንግሥት ያመጣብን ገዳይና ኢትዮጵያን በቁሟ እያለች ሰውነቷን አፈራረሶ የሚያጠፋት በሽታ ነው።
ወያኔ ካመጣው የፖለቲካ ቀውስ የተነሳ ሰዎች በአገሪቱ ከአንዱ ክልል ወደ ሌላው ክልል የመዘዋወር ነጻነታቸው ጠባብና ግዱብ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ከደቡብ ክልል ወደ አማራ ክልል ሄዶ መኖር ፣ መሥራት፣ መነገድ ይችላል? ከሰሜንም ክልል ወደ ምዕራብ ክልል ሄዶ በነጻነት መኖር የሚችልበት የዜግነት መብትም ሆነ የሕግ ዋስትና አለው? ኢትዮጵያ አለኝ የምትለው ዲሞክራሲ ይህንን ያረጋገጣል? ካልሆነ ለዚህ ሰው ኢትዮጵያ የምትባለዋ አገር የቷ ነች? የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ዴሞክራሲ የሚረጋገጠው በሕዝቦቿ አንድነት ከሆነ በተከፋፈለ ህዝብ የአገር ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ሊረጋገጥ የሚችለው እንዴት ነው? እስቲ ከአሜሪካ ፖለቲካ እንማር! አሜሪካ ከሁሉም የዓለም ዙሪያ የመጡ ሕዝቦች የሚኖሩባት አገር ብትሆንም አሜሪካውያን ሌላውን ሕዝብ በእኛ ላይ መጣችሁብን በሚል አንድም ቀን ተነስተውባቸው አያውቁም። ሁሉም ከአንዱ ግዛት ወደ ሌላው በመዘዋወር መሥራት፣ መማር፣ ቤት መግዛት ወዘተ የሚችሉበት መብታቸው የተጠበቀ ነው። በአገራችን ግን ዴሞክራሲ አለ ቢባልም በዴሞክራሲው ተጠቃሚዎቹ ፖለቲከኞችና ተከታዮቻቸው እንጂ ዜጋው አይደለም። የጐሳ ፖለቲካ ዜጋዎች በአገራቸው ውስጥ በየትኛውም ክልል በነፃነት የመንቀሳቀስና የመኖር ዋስትናቸውን የሚገድብ አደገኛ ሥርዓት ነው። የጐሳ ፖለቲካ ባለበት የሕዝቦች እኩልነት በሕልም ካልሆነ በውኑ አይታሰብም፣ አይሞከርምም። በአገራችን አለ የሚባለው የሕዝቦች እኩልነት በጦርነትና በጭፈራ ቀን እንጂ ሥልጣንን በመጋራት፣ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ወዘተ በማድረግ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን ለተወሰኑ ቡድኖች ጥቅም የቆመ፣ የአንዱን ወገን የበላይነትና የሌሎችን የበታችነት( Ethinic inequality)የሚያጎላ ነው። ግደይ በጠገበበት ገመዳ ጨፈረ ነው ነገሩ። የውጭ ኃይላት ወረራና ለዘመናት የነበረው ጦርነት ሊያፈርስ ያልቻለው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አንድነት በጐሳ ፖለቲካ እያፈራረሰ ይገኛል።
የጐሳ ፖለቲካ የመልካም አስተዳደርም (good governance) እንቅፋት ነው። መልካም አስተዳደር ማለት የአገሪቱን ዜጐች መብትን፣ ምጣኔ ሀብትን፣ ብሔራዊ ዋስትናን፣ የአገር ሉዓላዊነትን፣ የውጭ ግንኙነትን፣ ብዝሃ ህይወት፣ ትምህርትና ጤናን የአገር መከላከያንና ዳር ድንበርን ወዘተ በሚመለከት የሚደረስ ሚዛናዊ ውሳኔ ነው። በዚህ ዓይነቱ ውሳኔ ማዕከላዊ ተዋኒያን/ central figure / መንግሥት ነው። መልካም አስተዳደር ቢያንስ ቢያንስ ስምንት ባሕሪያት አሉት። አሳታፊነት Participatory/፣የጋራ ስምምነት/Concensus/ ተጠያቂነትaccountable፣ ግልጽነት transparency ፣ ምላሽ ሰጪነት rsponsiveness፣ ውጤታማነትና ብቃት effectiveness and efficiency ፣ ሁሉን ያማከለና በእኩልነት የተከተለ equitable and inclusiveness ፣ በውሳኔ አሰጣጡ ወቅት የህግ የበላይነትን የሚከተል follows the rule law,፣የአናሳዎችን አመለካከት የሚቀበል፣ የተጠቂዎችን ድምፅ የሚሰማና የማኅበረሰቡን የአሁኑናን የመጻኢውን ጊዜ ፍላጐት አጥኖ መላሽ የሚሰጥ ነው /the views of minorities is taken into account and the present and future need of the society are heared in decision making/ ። በቃላት ደረጃ በኢትዮጵያ መልካም አስተዳደር ና የሕግ የበላይነት እንዳለ በመንግሥት በኩል ቢወራም አመራሩ ግን የአምባገነናዊ ነው። ስለዚህ ይህች አገር መላ እሷነቷን እየፈራረሰ ካለው ከዚህ በሽታ ድና በሕይወት እንደትቀጥል፣ ከሕምሟም ነጻ እንድትሆን የመለኮት ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋታል። ይህም እንዲሆን ሁሉም ወደ አምላኩ መጮኸ ያለበት ጊዜ አሁን ነው።
፪. ሥርቆት፣ ጉቦና ዝርፊያ
ሌብነትና ጉቦ የአገራችን መጣኔ ሀብት የሚጐዳ ሕመም ነው። ምድሪቱ ታማለች ስንል ኢኮኖሚው ታሟል ማለታችን ነው። ይህ ጉዳይ በአንድ ወቀት በኢትዮጵያ ፓርላማ ተነስቶ ጥልቅ ውይይት እንደተደረገበት ሁሉም ኢትዮጰያዊ ያውቀዋል። ገዥው ፓርቲ የኢትዮጰያ ኢኮኖሚ ጤናማ ነው ሲል ተቃዋሚዎች ደግሞ ኢኮኖሚው በጣም ታማሚ ነው። እንዲያውም አንድ ቀን ተዝለፍልፎ ሊወድቅ ሁሉ ይችላል ብለው ምላሽ ሰጥተዋል። ወያኔ ወደ አገራችን እንደገባ የመጀመሪያው ያደረገው ነገር ቢኖር የአገሩን አንጡራ ሀብት እየዛቀ በሰዎች ኪስ መክተት ነው። ሕዝባችንን ያማረረ ያጐሳቆለ፣ ቢያንስ የዜግነት መብቱ በአግባብ እንዳይከበር ያደረገ ፣ ምድሪቱን ከዳር እስከዳር የሸፈነ አደገኛ ሕመም ቢኖር ጉቦና ሥርቆት ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት ጉቦ ወይም ሌብነት አይልም። ኪራይ ሰብሳቢነት ይለዋል። ካልሆነ ስኳር መላስ ይለዋል፣ ወይም ሙስና ይላል። ሙስናንና ኪራይ ሰብሳቢነትን እዋጋለሁ ይላል። ግን ሙስናውና ጉቦው መጠኑን እየጨመረ ሄደ እንጂ መፍትሔ አልተገኘለትም። በጉቦውና በሙስና የተዘፈቁት የመንግሥት አመራር አካላት፣ የፖሊቲካው ካድሬዎች፣ እና ገዥ ፓርቲ ያስቀመጣቸው የመመሪያ ኃላፊዎች በመሆናቸው ሕመሙ መድኃኒት ያልተገኘለት በዚህ ምክንያት ነው። እንዲያውም ሕመሟ ከጊዜ ወደ ጊዜም እየባሰ ሄደ። በቴሌቭዥኑና በራዲዮ ሙስናን እንዋጋ እያሉ ሕዝቡን ያጃጅላሉ። ሕዝቡ ጉቦ አይቀበል፣ መሬት የሚሸነሽነውና የሚሸጠው ተርታው ሕዝብ አይደለም፣ ወያኔና የወያኔ ካድሬዎች እንጂ! የህዝብና የመንግሥት ገንዘብ እየዘረፉ ኪሳቸው እየከተቱ በአጭር ጊዜ ሚሊየነር እየሆኑ ያሉትን ቁልፍ መሪዎችን ከእኩይ ተግባራቸው እንዲቆጠቡና እጃቸውን እንዲሰበስቡ መናገር ያለበት ለእነርሱ ሆኖ ሳለ በሌቦች እየተዘረፈ ያለውን ሚስኪን ሕዝብ ሙስናን ተዋጉ ይላል። ቀልድ ቢባል በሕዝብ ላይ መቀለድ አንድ ቀን ዋጋ ማስከፈሉ አይቀርም። የኢህአዴግ መንግሥት ጠላትን አሸንፌአለሁ የሚል፣ ከራሱ አልፎ የሌላውን አገር ሰላም አስጠብቃለሁ የሚል፣ በአፍሪካ ቀንድ በጐም ይሁን አሉታዊ ተጽዕኖ የማምጣት ብቃት አለኝ የሚል መንግሥት ነው። ይህ ሁሉ ብቃት ኖሮት ሀዝቦቿን የሚቦጠቡጠውን ሙሰኛ አደብ እንዲገዛ ያላደረገው አቅም አንሶት ሳይሆን መንግሥትራሱ ሙሰኛ ስለሆነ ነው። ያለ ጉቦ የሚፈጸም ጉዳይ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደሌለ በአመራር መዋቅሩ ከላይ እስከታች ያሉ እያንዳንዱ ያውቃል። የትኛውም ቀላል ይሁን ከባድ ጉዳይ ያለ ጉቦ አይከናውንም። የሚከናወንላቸው ለወያኔዎችና ለፖለቲካ ድጋፊዎች ብቻ ነው። አገሪቱ የእነርሱ እንጂ የዜጋው አይደለችም። መነገድ የሚችሉት ወያኔዎችና የፖለቲካው ደጋፊዎች ብቻ ሲሆኑ ንግዳቸውን ሲነግዱም ሆነ ሲሸጡ ቀረጥ የማያስበረግጋቸው ናቸው። ዜጋው ግን የንግድ ፈቃድ ቢኖረውም ያንኑን ለማግኘት የሚከፍለው ጉቦ ሌላ ድርጅት ሊያራምድ ይችላል። በመሣሪያ አስፈራረቶም ሆነ ሰዓት እላፊ አወጆ የአገሪቱን አንጡራ ሀብት ማጋዝ ሥራዬ ብሎ ተያይዞታል። እግዜር የለሹ የደርግ መንግሥት ወንበዴ የሚል ስም የሰጠው ለዝርፊያ ያለውን መቋመጥ ስለታዘበው ይሆናል። አሁን ምድራችን በዝርፊያ የታምሰች ናት። እናት አገራችንን ብንወዳትም፣ በሰፈነባት እንደ ባህል እየተገነባ ባለው ሌብነትና ዝርፊያ እናፍራለን። ሌባ እናት በሰረቀች ቁጥር ልጆቿ ይሸማቀቃሉ፣አንገታቸውንም ይደፋሉ።
ነቢያት ስለ ኢኮኖሚው እድገት ይናገራሉ። መጻሕፍትም እየተጻፉ ናቸው። በየመድረኩ የምንሰማው ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ይባርካታል የሚል ነው። አንዳንዶቹ ሌሎች የሚሉትን ሰምተው እንጂ በእርግጥም እግዚአብሔር ተናግአቸው አይደለም። በአገራችን የምንሰማው ትንቢት አብዛኛው የነቢያቶቹ የግል ምኞታቸው ነው እንጂ እግዚአብሔር የሚሰጣቸው መልእክት አይደለም። ምኞትና መልእክት ይለያያል።
3ኛ. ውሸትና ማታለል፡
መንግሥታችን ልማታዊ ነኝ ይላል ግን አይደለም። ዴሞክራት ነኝ ቢልም ዴሞክራሲው የማስመሰል፣የፖለቲካ ሽፋን ለማግኘት ሲል የሚያደርገው የቃላት ቅመማ ነው። በአገራችን ኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ቢኖርም ያ ሕገ መንግሥት የበላይ አይደለም። በአንድ ቀን ጉቦ ሊናድ የሚችል በአሸዋ ላይ እንደተሠራ ቤት ነው። እውነት እንነጋገር ካልን በአገራችን ላይ የመሪዎችና የካድሬዎች የበላይነት እንጂ የሕግ የበላይነት የለም። የኢሀአዴግ መንግሥት የሕገ መንግሥቱን ሥርዓት በሃይል ለመናድ የሚሹ ኃይሎች እያለ በሌሎች ላይ የሚፈረድ ቢሆንም ውሸትን እውነት አስመስሎ በመናገር የኢትዮጵያ መሪዎችን የሚያክል የለም። አንዱ ጄኔራል ሲናገሩ፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር የወያኔን ሠራዊት ይወደዋል ያፈቅረዋል ማለታቸው ብቻውን ለዚህ ማሳያ ነው። ክ1997 ምርጫ ጋር በተያያዘ በተነሳው ረብሻ በመንግሥት ታጣቂዎች የተገደሉ ስዎች ጉዳይ ሲነሳ የመንግሥት ባልሥልጣናት መልስ ሲሰጡ ሰዎቹ የሞቱት ባንክ ሲዘርፉ ነው ማለታቸው ሌላው ማሳያ ነው። አፈሩን ገለባ ያርግላቸውና የሞቱ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ደመወዛቸው ስድስት ሺህ ብር ብቻ ስለሆነ ባለቤታቸው ያንን እንደምንም አብቃቅተው እንደሚኖሩና በዓለም ላይ የመጨረሻ ዝቅተኛ ገቢ ያለው ሰው ማነው ቢባል እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸውን መስማታችን እንደ ተጨማሪ ማሳያ እንውሰድ። በምዕራቡ በኩል መሬት ለሱዳን ሊሰጥ የኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈራረመ ያለው ለምንድነው ሲባል ለሱዳን ምንም መሬት አልተሰጠም፣ አንድም የኢትዮጵያ ገበሬ ከቦታው አልተፈናቀለም ማለቱ ሌላው ተጨማሪ ማሳያ ነው። መንግሥታችን ይህን ሁሉ እያለ መሬቱን ግን አሳልፎ እያሰጠ ነበር። ቴሌቭዝኑና ራዲዮ ቢሆን የኢህአዴግ መንግሥት ልሳን ስለሆነ እውነት ተናገረ ቢባል ሰዓት ብቻ ነው። ፖለቲካ በራሱ የቆሸሸ ጨዋታ ቢሆንም አሁን አመራር ላይ ያለውን መንግሥት ተከትሎ ወደ አገራችን የገባው የውሸት መንፈስ ግን የትም የሌለ ነው።
4ኛ. ሰብአዊ መብት ረገጣ
በዓለም አቀፍ ደረጃ የታውቁ የሰብአዊ ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን የመብት ረገጣ መስማት እጅግ የሚዘገንን ነው። በተለይም ከብሔራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሠራዊት በሚወስደው ከመጠን በሚያልፍ እምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹህ ዜጎች ሕይወት ይቀጠፋል። የኢህአዴግ መንግሥት ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ ወዲህ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር መገመት ከሚቻለው በላይ ነው። በሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ወቅት ብቻ ሕይወት የመንግሥት ታጣቂዎች በወሰዱት ተመጣጣኝ ባልሆነ የግፍ ርምጃ ክ500 በላይ ንጹሐን ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል። አምኔስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት እንደሚገልጸው ከ2015( እ ኤ አ) ጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ 800 ስዎች ተገድሏል። ከዚህም በተጨማሪ መንግሥት አስታጥቆ በሕብረተሰቡ ውስጥ ያሰማራቸው ሠራዊት በንጹሐን ላይ የሚያደርሱት ከመጠን ያለፈ ጥቃት ዓለምን ሁሉ ያንገሸገሸ ነው። ምንም የፖለቲካ አቋም የሌላቸውንም ጨምሮ ያለ ፍርድ ቤት ውሳኔ ያለ ጠያቂ በእሥር ማጎር፣ ማሰቃየት፣ መገረፍ ፣ስብዕናን የሚያዋርዱ ቅጣቶችን ማድረስ ፣ ያሉበት እንዳይታወቅ ማደረግ ወዘተ ይገኙበታል። አሁን ያለ የአገራችን ስብአዊ መብት ረገጣ በየትኛውም ዘመናትና አገዛዝ ያልነበረ መሆኑ ግልጽ ነው።
ይህ በሽታ እየሰፋና መጠኑን እየጨመረ መሄዱ በሁሉም ዘንድ የታወቀ ነው። ይህቺን አገር ከዚህ ችግር የሚያላቅቃት መፍትሔ ፣ የበሽታዋም መድኃኒት ከየት ይመጣ? ከተባበሩት መንግሥታት? ከልዕለ ኃያሏ አሜሪካ? ከአፍሪካ ሕብረት? ወይስ ከአውሮፓ ህብረት? ኢትዮጵያን ለመፍትሔ ፍለጋ በአሜሪካን አገር ከጮኹ፣ መንገድ አጣብበው ኡኡታና እሪታ ካበዙ ዘመን የለውም። አሁን አሁን እሱም ተከልክሏል ወይ እነርሱ ስልችቶአቸው ተውት መሰለኝ ጋብ ብሏል። በሰማይ ንጉሥ በእግዚአብሔር እጅ ግን መፍትሔ አለ። እርሱ በሰዎች ልጆች መንግሥት የሚሰለጥን ነው። ምድራችሁን እፈውሳለሁ ያለው እርሱ ስለሆነ መፍትሔና መላ ፍለጋ በእርሱ ደጅ እሪ እንበል፣ ኡኡታም እናሰማ። እርሱ ምድራችንን የፈውሳታል ፣ ለገዥዎቻችንም ልቦና ይሰጣቸዋል፣ የሕዝባችን እምባና የግፍ የሚፈሰው ደም ያበቃል። የአገራችን ጉዳይ ፈውስ የሚያስፈልገው ሕመም በመሆኑ ለመድኃኒትጥ ፍለጋ መሮጥ አለብን። መድኃኒቱ በጦርነት አይገኝም፣የሃያላን አገሮች ቢሮ በር ላይ ተሰባስበው እሪታ በማሰማትም አይገኝም። መድሓኒቱ እንዲገኝ በፍጹም ልብ ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ፊቱን ስንፈልግ ብቻ ነው። የአገራችን ፈውስ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ ከሌላ ቦታ ከየትም አይመጣምና። እግዚአብሔር አገራችንን የጐሳ ፖለቲካ፣ ሥርቆትና ዝርፊያ፣ውሸትና ማታለል እና ሰብአዊ መብት ረገጣ ከተባሉት ሥር የሰደዱ በሽታዎች አገራችንን ይፈውሳት! አሜን እንበል።
እንደዚሁም ሁሉ ምድርም ለሕይወት በሚያሰጋ በከባድ በሽታ ትታመማለች። ስለዚህም ነው እግዚአብሔር ምድራችሁን እፈውሳለሁ ያለው። ሰው ሲታመም ወደ ሐኪም ቤት ይወሰዳል። ምድር ስትታመም ግን ከመለኮት ጣልቃ ገብነት በቀር ሌላ ሐኪም ቤት የለም። ምድር ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ምን ሐኪም የላትም። መድሃኒቱም ያለው በእርሱ እጅ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ መታመሟን ያወቅነውም ብዙ ቆይተን አሁን በቅርቡ ቢሆንም እኛም አብረን እየታመምን ነው። ስለዚህ ይህቺን አገር የሚወዳት ሁሉ ሊጸልይላት ይገባዋል። የአገሬ ፍቅር አለኝ የሚል ማንም ከሚዘፍንላት ይልቅ ፣ ከሚዘምርላትም ይልቅ ፣ አሁን የሌላትን መንፈሳዊ ስም ከሚስጣት ይልቅ ሊጸልይላት ይገባዋል። ስለዚህች አገር ማቅ ለብሰን ፣ አመድም ነስንሰን ፣ ከካህን እስከ ምዕመን ቢቻል በር ዘግተን ፣ ከእህል ከውሃ ተለይተን ማልቀስና መቃተት ያለብን ጊዜ ቢኖር አሁን ነው። ሕመሞቿን በቀላል አማርኛ ፣ እንደሚከተለው እንድገልጽ ይፈቀድልኝ።
፩. በዘርና በጐሳ የሚከፋፍል ሕመም።
እስትሮክ አንዱን የአካል ክፍል ለይቶ የሚጐዳ የህመም ዓይነት ነው። ይህ ቀኙ እየሠራ ግራውን እንዳይንቀሳቀስ የሚያደርግ ወይም ግራው ደህና ሳለ የቀኙን በኩል ከላይ እስከታች የሚያሽመደምድ በሁሉ የተረገመ በሽታ ነው። ። ይህ ዓይነቱ በሸታ ቶሎ ባይገድልም የሕመምተኛውን የመዳን ተስፋ ያጨልማል። እንደዚሁም የአገራችን ሕመም በዘር በጐሳ፣ በወገን፣ በክልል የሚከፋፈል እንደ ስትሮክ ዓይነት ነው። ሌሎች የበለጠጉና ያደጉ አገሮች የጐሳ ፖለቲካን /Ethnic politics/ በጐጂነቱ ፈርጀው ወደ እንጥሮጦስ ከጣሉና ዳግም ተንስቶ ለአገራቸውና ለሕዝባቸው ጥፋት እንዳያመጣ መንገዱን በጥርብ ድንጋይ ከዘጉ በኋላ ይህ አደገኛ ፖለቲካ በአገራችን የዕድገት፣ የዴሞክራሲና የልማት አምድና ምሶሶ ተደርጐ ተወስዷል። ኢትዮጵያ የብዙ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የቋንቋዎች፣ የባህሎች ፣ የዘርፈ ብዙ ማህበራዊ እሴቶች ባለቤት መሆኗ ከፍሎ ለሚያሰቃይ በሽታ ምቹ አድርጐአታል። የአገራችን ሕዝቦች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት እንደጌጥ እየቆጠሩ እርስ በእርሳቸውም እየተቻቻሉ ፣ በአካባቢቸውም ያለውን ግብአት በጋራ እየተጠቀሙ ያለ አንዳች መገፋፋት ለዘመናት መኖራቸው፤ ሰሜኑ ከደቡቡ ሕዝብ፣ ምሥራቁ ከምዕራቡ፣ የመሀሉ ከዳሩ ሕዝብ ጋር ተረዳድተውና ተከባብረው የኖሩባትና የሚኖሩባት አገር መሆኗ እውን ቢሆንም አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ባመጣብን ከፋፋይ ፖለቲካ የተነሳ ሕዝቦቿ እርስ በርሳቸው ከመከፋፈልም አልፎ እስከ መገዳደል ደርሰዋል። ሥር የሰደደ በሽታ የሰውን የቀድሞ መልኩን እንደሚለውጠው ሁሉ አሁን ያለችው ኢትዮጵያ ድሮ የምትታወቀዋ በታሪክ ስለ እርሷ የምንሰማው፣ምሁራን ያስቀሩልንን ታሪክ የምናነበው ሳይሆን ታሪኳ ተቀይሮ፣ መልኩዋም ጠፍቶ ፣ ከቀደሞው ታሪክ ጋር የማይገጥም እንግዳ ነገር እንድናይ የሚያደርግ ሕመም ሥር እየሰደደባት ነው።
በአገሪቱ ያለው እያንዳንዱ ብሔር መነሻ ማንነት ቢኖረውም በቅድሚያ ሰው መሆኑን ያምናል፣ከዚያም ኢትዮጵያዊ መሆኑን ያምናል። አማራው አማራ ነኝ ቢልም ኢትዮጵያዊነቱን አይክድም ነበር። የበላይ ዘለቀ ልጅ ጐጃሜ ነኝ፣ ደግሞም ምንጃሬ፣ ሸንኮራ ነኝ ዘራፍ፣ዘራፍ ዘራፍ ቢልም ኢትዮጵያዊነቱን ሳይክድና ሳይለቅ ከሌላው ሕዝብ ጋር እርሱም አብሮ ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ያምን ነበር። ሌላው ብሔር ቢሆንም እንደዚያው ነው። የአባጁራፍ ልጅ ኦሮሞ ነኝ ፣ የካዎ ጦና ልጅ ወላይታ ነኝ፣ የንጉሥ አይማሎ ልጅ ጋሞ ነኝ፣ የንግሥት ፉራ ልጅ ሲዳማ ነኝ ወዘተ ቢልም ከሌሎች ሕዝቦች ጋር ኢትዮጵያዊ ነኝ፣ አገሪቱ የጋራችን ነች፣ ወንዙ ሸንተረሩ ተራራው፣ ጋራው፣ ሁሉ የጋራችን ነው፣ እያለ በልዩነቱ ውስጥ ያለውን ውበትና ጣዕም እያጣጣመና እያደነቀ፣ አንዱ የሌላውን ሕመም እየታመመ፣ በደስታውም አብሮ እየተደሰተ፣ ኢትዮጵያን በጋራ ተሸክሞ የኢህአዴግ መንግሥት አገሪቱን እስከሚቆጣጠርበት ጊዜ አደረሳት። ያውም ክብሯ ዝቅ ሳይል፣ ዳር ድንበሯ ሳይደፈር፣ አንድ ስንዝር መሬት ለጐረቤት አገር በድርድርም ሆነ ጦርን በመፍራት አሳለፎ ሳይሰጥ ነው ታዲያ! የኢህአዴግ መንግሥት ምድሩን ማስተዳደር ሲጀምር አፉን የፈታው “መገንጠል” ፣ “ክልል”፣ “የራስን መብት በራስ መወስን” በሚሉ ቃላቶች ነው። ቃላቶቹ/ አሳቦቹ ልበላቸው/ ለኢትዮጰያ ሕዝቦች አንድነትና እኩልነት ፣ ለመብታቸውም መከበር ዘብ የሚቆሙ ቢመስሉም አሁን ለሚታየው መከፋፈልና መናቆር የተጣሉ የመሠረት ድንጋዮች ናቸው። ቃላቶቹ አሳችና ግራ አጋቢዎች ናቸው። አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት የሕዝቦችን ትሥሥር ለመበጣጠስ የቻለው በእነዚህ የመሠረት ድንጋዮች ላይ ቆሞ ነው። ይህ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ አንዱን ብሔር ከሌላው፣ አንዱን ክልል ከአንዱ ጋር የሚያባላው እነዚህን በሽታ አምጪ ሕዋስ የሆኑ ቃላቶችን በምድሪቱ ላይ በመበተን ነው። ይህም በመሆኑ ኢትዮጵያ ከተፈጠረችበት ጊዜ አንስቶ እስከአሁን ድረስ ተቻችለው የኖሩ፣ ተሳስበው፣ ተከባብረው፣ ተጋብተውና ተዋልደው ፣ በሁሉም ማኅበራዊ ጉዳዮች አንድ ሆነው በመልካም ትሥሥር ለዘመናት የቆዩ ሕዝቦች እርስ በርሳቸው ለመጐሻሸም፣ ለመገዳደል ፣ ለመፈነቃቀልና ለማሳደድና ለመሰደድ ከተጋለጡ ይኸው የአንድ ጎልማሳ ዕድሜ እያስቆጠሩ ነው። ለዚህ ሕመሟ መድኃኒት ያልተገኘላት አገራችን ሕመሟ እየጠናባት በመሆኑ መድኃኒትና መላ ፣ መፍትሔም ያስፈልጋታል። ከመጀመሪያውም መፍትሔ ሊገኝ በማይችል ሁኔታ መርዙ ስለተቀነባበረና በየቦታውም ስለተቀበረ ሕመሟ እየባሰባት መጣ። የኢሀአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝቦች በአንድነት እንዳይኖሩ በቋንቋና በብሔር እንዲከፋፈሉ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የሳለው የአገሪቱ ካርታና ክልላዊ መዋቅሩ እንኳ ቢታይ ብሔርን ባህልንና ቋንቋን መሠረት ያደረገ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ወደፊት አንዱ ከሌላው ለመገንጠል እንዲያመቸው ሆን ተብሎ የተሠራ ተንኮል መሆኑ ሳይገባን ኖረናል። በአሁኑ ጊዜ መቻቻልን ትተው ወንድም ወንድሙን በጦር እያሳደደ፣ ክልሌ ስለሆነ በዚህ አካባቢ መኖር ፣ መንቀሳቀስ ፣ መሥራት ወዘተ አትችልም እያለ አብሮት የኖረውን፣ አብሮት ያደገውን ያሳድደዋል። ሁለት ሰዎች ቢጣሉና አንደኛው ቢጐዳ እነማን ናቸው የተጣሉት ተብለው በሰውነታቸውና በስማቸው መሠረት መጠየቅና ማስረዳት አግባብ ሆኖ ሳለ አሁን የሚጠይቀው ብሔር ፣ ዘር ወይም ክልል ነው። ይቀጥልና የዚህ ብሔር የዚኛውን ብሔር ደበደበ፣ ወይም የዚህ ብሔር የዚኛውን ብሔር ገደለ ይባልና ጠቡ የብሔር ይሆናል። አሁንም ይቀጥልና ይህ ብሔር ከዚኛው ብሔር ጋር ተጣላ፣ ከዚሀ ብሔር ይህን ያህል ሰው ሞተ፣ ይህን ያህል ሰው ተጐዳ የሚል ዜና ይሰራጫል። ወያኔ ሕዝባችንን እጁን ይዞ ሀ ሁ ሂ እያለ ፊደል ያስቆጠረውና ያለማመደው ይህንን ክፉ ሥራ ነው። የግለሰቦቹ ጠብ ዕለታዊ ጉዳይ የግል እንጂ የብሔር ጠብ አልነበረም ግን የተዘረጋው መዋቅር እና የተቀመመው የፖለቲካ መርዝ ይህንን መሰል በሽታ በሕዝባችን ላይ አመጣ። እውነት ለመናገር አንዱ ሕዝብ አብሮት ከኖረው፣ በባህል ፣ በሃይማኖት በጋብቻ ወዘተ ተሳስሮ፣ ተቀላቅሎ፣ አንዱ ከሌላው ጋር ተጋብቶና ተዋልዶ ለዘመናት ከኖረበት ከሌላው ህዝብ ጋር መጋጨትም ሆነ መቃቃር እንደሚገባው የሚያምን ኢትዮጵያዊ የለም። የአማራ ሕዝብ ከሮሞና ከሌላው የሲዳማ ሕዝብ ከወላይታ ህዝብ ጋር ፣ ጉጂ ከቡርጂ ጋር መተላለቅ አይገባውም ነበር። በቅርቡ እንኳ በዝዋይ ከተማ በሁለት ኢትዮጵያውያን መካከል ጠብ ቢፈጥር የኦሮሞና የወላይታ ሕዝቦች ግጭት ተደርጐ መወሰዱ ፣ አሁን ደግሞ በምሥራቁ የአገራችን ከፍል የብዙዎችን ሕይወት እየቀጠፈ ያለው ቀውስ እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ የሚችል ነው። ሕመሙ በኢትዮጵያ መላ ሰውነቷ ላይ ስለተሠራጨ ይህ አሳዛኝ ነገር ሊሆን ቻለ። የኢህአዴግ ወያኔ መንግሥት መሪዎች አሸናፊውን ለመለየት በመሀል እንዳለ ታዛቢ ነገሩን በትዝብት ያዩታል ወይም እንደ ተመልካች ይዝናኑበታል እንጂ መፍትሔ አይሰጡበትም፤ የጸጥታ ሃይሉም ሬሳ ቆጥሮ ሪፖርት ያደርጋል እንጂ በሚተላለቀው ሕዝብ መካከል ገብቶ የሕዝቡን ዋስትና አያረጋግጥም፣ ምክንያቱም ፖሊቲካው ሲጠነሰስ የተፈለገው ይኸው ነውና። ይህ በሽታ ኢትዮጵያን እንዳያጠፋት የተቻለውን መፍትሔ ሁሉ መፈለግ ያሻል። ከመፍትሔዎቹ አንዱና ቀዳሚው በእግዚአብሔር ፊት ማልቀስ ነው። ያለዚያ አሁን የተበተነው ሕመም አመንጪ የፖለቲካ ሕዋስ አካሉዋን በጣጥሶና ገነጣጥሎ ይጨርሰዋል። መንግሥት እንደሆነ የኢትዮጵያን መሬት ሲያሻው ለጐረቤት አገር እየሸጠ ፣ ሲያስፈልገው ከመሃሉ አርሶ አደሩን አፈናቅሎ መሬቱን ለባዕድ እየሸጠ ሕዝባችን ላይ ድራማ ይሠራበታል፣ ቁማርም ይጫወትበታል። በምዕራቡ በኩል አንድ የአካል ክፍል ተቆርሶ ወደ ሱዳን በኩል ወድቋል። የነገ ተረኛ ማን እንደሆነ አናውቅም።
አካልን የሚደመስሰው የፖለቲካ ሕዋስ በቤተመንግሥት ብቻ ሳይወሰን ወደ ሃይማኖቱ ውስጥም መግባቱ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕጣ፣ በሕይወትም የመቆየቷን ጉዳይ የበለጠ አሳሳቢ አድርጐታል። ቸር ወሬ ያሰማን እንጂ ቤተክርስቲያንም በዘር ፣ በጐሳ ከተከፋፈለች ጊዜ የለውም። እንዲያውም ፈጥና ራሷን የሰባበረችው ቤተ ክርስቲያን ነች። በብሔር ወገንተኝነት ላይ የተመሠረተ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ አለ። መንግሥትም ለመከፋፈል ዓላማው እንዲያመቸው በሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የራሱ ካድሬዎች ሰግስጓል። በየእምነት ተቋማት ውስጥ የኢህአዴግ የደህንነት ካድሬዎች አሉ። የፖለቲካ መዋቅሩ ከመንግሥት ተቋማት እስከ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ድረስ ተዘርግቷል። የወንጌል ቃል በሚገለጥበት ሥፍራ ላይ ቆመው መንግሥትን የማሞካሸት የሚቃጣቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች ጥቂት አይደሉም።
የሕመም አምጪው ሕዋስ በአገር ቤት ብቻ ሳይወሰን ባህር ተሻግሮ በመምጣት ሕዝቦቿን እያተራመሳቸው ነው። ከቤተሰቦቻቸው ጋር በልጅነታቸው ከአገር የወጡ ልጆች የመጡበትን አገር ሲናገሩ ከምሥራቅ አፍሪካ ፣ ከኦሮሚያ ነው የመጣነው ሲሉ ከኢትዮጵያ ናችሁ ሲባሉ አይደለም ከኦሮሚያ ነው ይላሉ። እንግዲህ እነዚህ ልጆች ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንዳለች አያውቁም ማለት ነው። ከእነርሱ በኋላ የሚመጣው ትውልድ ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንደነበረች አድርገው እንደ ታሪክ መናገራቸው አይቀርም። ጂቡቲ ከኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገራት አንዷ እንደነበረች የማያውቅ ወጣት ብዙ እንደነበረ ሁሉ ኦሮሚያ ፣ አማራ፣ ሐሬሪ፣ ቤንሻንጉል ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ ወዘተ የሚባሉት አገሮች እንደ አንድ አገር በአንድ መንግሥት አስተዳደር ሥር ነበሩ እያሉ ማውራታቸው አይቀሬ ነው። ይህ የዘመኑ መንግሥት ያመጣብን ገዳይና ኢትዮጵያን በቁሟ እያለች ሰውነቷን አፈራረሶ የሚያጠፋት በሽታ ነው።
ወያኔ ካመጣው የፖለቲካ ቀውስ የተነሳ ሰዎች በአገሪቱ ከአንዱ ክልል ወደ ሌላው ክልል የመዘዋወር ነጻነታቸው ጠባብና ግዱብ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ከደቡብ ክልል ወደ አማራ ክልል ሄዶ መኖር ፣ መሥራት፣ መነገድ ይችላል? ከሰሜንም ክልል ወደ ምዕራብ ክልል ሄዶ በነጻነት መኖር የሚችልበት የዜግነት መብትም ሆነ የሕግ ዋስትና አለው? ኢትዮጵያ አለኝ የምትለው ዲሞክራሲ ይህንን ያረጋገጣል? ካልሆነ ለዚህ ሰው ኢትዮጵያ የምትባለዋ አገር የቷ ነች? የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ዴሞክራሲ የሚረጋገጠው በሕዝቦቿ አንድነት ከሆነ በተከፋፈለ ህዝብ የአገር ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ሊረጋገጥ የሚችለው እንዴት ነው? እስቲ ከአሜሪካ ፖለቲካ እንማር! አሜሪካ ከሁሉም የዓለም ዙሪያ የመጡ ሕዝቦች የሚኖሩባት አገር ብትሆንም አሜሪካውያን ሌላውን ሕዝብ በእኛ ላይ መጣችሁብን በሚል አንድም ቀን ተነስተውባቸው አያውቁም። ሁሉም ከአንዱ ግዛት ወደ ሌላው በመዘዋወር መሥራት፣ መማር፣ ቤት መግዛት ወዘተ የሚችሉበት መብታቸው የተጠበቀ ነው። በአገራችን ግን ዴሞክራሲ አለ ቢባልም በዴሞክራሲው ተጠቃሚዎቹ ፖለቲከኞችና ተከታዮቻቸው እንጂ ዜጋው አይደለም። የጐሳ ፖለቲካ ዜጋዎች በአገራቸው ውስጥ በየትኛውም ክልል በነፃነት የመንቀሳቀስና የመኖር ዋስትናቸውን የሚገድብ አደገኛ ሥርዓት ነው። የጐሳ ፖለቲካ ባለበት የሕዝቦች እኩልነት በሕልም ካልሆነ በውኑ አይታሰብም፣ አይሞከርምም። በአገራችን አለ የሚባለው የሕዝቦች እኩልነት በጦርነትና በጭፈራ ቀን እንጂ ሥልጣንን በመጋራት፣ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ወዘተ በማድረግ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን ለተወሰኑ ቡድኖች ጥቅም የቆመ፣ የአንዱን ወገን የበላይነትና የሌሎችን የበታችነት( Ethinic inequality)የሚያጎላ ነው። ግደይ በጠገበበት ገመዳ ጨፈረ ነው ነገሩ። የውጭ ኃይላት ወረራና ለዘመናት የነበረው ጦርነት ሊያፈርስ ያልቻለው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አንድነት በጐሳ ፖለቲካ እያፈራረሰ ይገኛል።
የጐሳ ፖለቲካ የመልካም አስተዳደርም (good governance) እንቅፋት ነው። መልካም አስተዳደር ማለት የአገሪቱን ዜጐች መብትን፣ ምጣኔ ሀብትን፣ ብሔራዊ ዋስትናን፣ የአገር ሉዓላዊነትን፣ የውጭ ግንኙነትን፣ ብዝሃ ህይወት፣ ትምህርትና ጤናን የአገር መከላከያንና ዳር ድንበርን ወዘተ በሚመለከት የሚደረስ ሚዛናዊ ውሳኔ ነው። በዚህ ዓይነቱ ውሳኔ ማዕከላዊ ተዋኒያን/ central figure / መንግሥት ነው። መልካም አስተዳደር ቢያንስ ቢያንስ ስምንት ባሕሪያት አሉት። አሳታፊነት Participatory/፣የጋራ ስምምነት/Concensus/ ተጠያቂነትaccountable፣ ግልጽነት transparency ፣ ምላሽ ሰጪነት rsponsiveness፣ ውጤታማነትና ብቃት effectiveness and efficiency ፣ ሁሉን ያማከለና በእኩልነት የተከተለ equitable and inclusiveness ፣ በውሳኔ አሰጣጡ ወቅት የህግ የበላይነትን የሚከተል follows the rule law,፣የአናሳዎችን አመለካከት የሚቀበል፣ የተጠቂዎችን ድምፅ የሚሰማና የማኅበረሰቡን የአሁኑናን የመጻኢውን ጊዜ ፍላጐት አጥኖ መላሽ የሚሰጥ ነው /the views of minorities is taken into account and the present and future need of the society are heared in decision making/ ። በቃላት ደረጃ በኢትዮጵያ መልካም አስተዳደር ና የሕግ የበላይነት እንዳለ በመንግሥት በኩል ቢወራም አመራሩ ግን የአምባገነናዊ ነው። ስለዚህ ይህች አገር መላ እሷነቷን እየፈራረሰ ካለው ከዚህ በሽታ ድና በሕይወት እንደትቀጥል፣ ከሕምሟም ነጻ እንድትሆን የመለኮት ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋታል። ይህም እንዲሆን ሁሉም ወደ አምላኩ መጮኸ ያለበት ጊዜ አሁን ነው።
፪. ሥርቆት፣ ጉቦና ዝርፊያ
ሌብነትና ጉቦ የአገራችን መጣኔ ሀብት የሚጐዳ ሕመም ነው። ምድሪቱ ታማለች ስንል ኢኮኖሚው ታሟል ማለታችን ነው። ይህ ጉዳይ በአንድ ወቀት በኢትዮጵያ ፓርላማ ተነስቶ ጥልቅ ውይይት እንደተደረገበት ሁሉም ኢትዮጰያዊ ያውቀዋል። ገዥው ፓርቲ የኢትዮጰያ ኢኮኖሚ ጤናማ ነው ሲል ተቃዋሚዎች ደግሞ ኢኮኖሚው በጣም ታማሚ ነው። እንዲያውም አንድ ቀን ተዝለፍልፎ ሊወድቅ ሁሉ ይችላል ብለው ምላሽ ሰጥተዋል። ወያኔ ወደ አገራችን እንደገባ የመጀመሪያው ያደረገው ነገር ቢኖር የአገሩን አንጡራ ሀብት እየዛቀ በሰዎች ኪስ መክተት ነው። ሕዝባችንን ያማረረ ያጐሳቆለ፣ ቢያንስ የዜግነት መብቱ በአግባብ እንዳይከበር ያደረገ ፣ ምድሪቱን ከዳር እስከዳር የሸፈነ አደገኛ ሕመም ቢኖር ጉቦና ሥርቆት ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት ጉቦ ወይም ሌብነት አይልም። ኪራይ ሰብሳቢነት ይለዋል። ካልሆነ ስኳር መላስ ይለዋል፣ ወይም ሙስና ይላል። ሙስናንና ኪራይ ሰብሳቢነትን እዋጋለሁ ይላል። ግን ሙስናውና ጉቦው መጠኑን እየጨመረ ሄደ እንጂ መፍትሔ አልተገኘለትም። በጉቦውና በሙስና የተዘፈቁት የመንግሥት አመራር አካላት፣ የፖሊቲካው ካድሬዎች፣ እና ገዥ ፓርቲ ያስቀመጣቸው የመመሪያ ኃላፊዎች በመሆናቸው ሕመሙ መድኃኒት ያልተገኘለት በዚህ ምክንያት ነው። እንዲያውም ሕመሟ ከጊዜ ወደ ጊዜም እየባሰ ሄደ። በቴሌቭዥኑና በራዲዮ ሙስናን እንዋጋ እያሉ ሕዝቡን ያጃጅላሉ። ሕዝቡ ጉቦ አይቀበል፣ መሬት የሚሸነሽነውና የሚሸጠው ተርታው ሕዝብ አይደለም፣ ወያኔና የወያኔ ካድሬዎች እንጂ! የህዝብና የመንግሥት ገንዘብ እየዘረፉ ኪሳቸው እየከተቱ በአጭር ጊዜ ሚሊየነር እየሆኑ ያሉትን ቁልፍ መሪዎችን ከእኩይ ተግባራቸው እንዲቆጠቡና እጃቸውን እንዲሰበስቡ መናገር ያለበት ለእነርሱ ሆኖ ሳለ በሌቦች እየተዘረፈ ያለውን ሚስኪን ሕዝብ ሙስናን ተዋጉ ይላል። ቀልድ ቢባል በሕዝብ ላይ መቀለድ አንድ ቀን ዋጋ ማስከፈሉ አይቀርም። የኢህአዴግ መንግሥት ጠላትን አሸንፌአለሁ የሚል፣ ከራሱ አልፎ የሌላውን አገር ሰላም አስጠብቃለሁ የሚል፣ በአፍሪካ ቀንድ በጐም ይሁን አሉታዊ ተጽዕኖ የማምጣት ብቃት አለኝ የሚል መንግሥት ነው። ይህ ሁሉ ብቃት ኖሮት ሀዝቦቿን የሚቦጠቡጠውን ሙሰኛ አደብ እንዲገዛ ያላደረገው አቅም አንሶት ሳይሆን መንግሥትራሱ ሙሰኛ ስለሆነ ነው። ያለ ጉቦ የሚፈጸም ጉዳይ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደሌለ በአመራር መዋቅሩ ከላይ እስከታች ያሉ እያንዳንዱ ያውቃል። የትኛውም ቀላል ይሁን ከባድ ጉዳይ ያለ ጉቦ አይከናውንም። የሚከናወንላቸው ለወያኔዎችና ለፖለቲካ ድጋፊዎች ብቻ ነው። አገሪቱ የእነርሱ እንጂ የዜጋው አይደለችም። መነገድ የሚችሉት ወያኔዎችና የፖለቲካው ደጋፊዎች ብቻ ሲሆኑ ንግዳቸውን ሲነግዱም ሆነ ሲሸጡ ቀረጥ የማያስበረግጋቸው ናቸው። ዜጋው ግን የንግድ ፈቃድ ቢኖረውም ያንኑን ለማግኘት የሚከፍለው ጉቦ ሌላ ድርጅት ሊያራምድ ይችላል። በመሣሪያ አስፈራረቶም ሆነ ሰዓት እላፊ አወጆ የአገሪቱን አንጡራ ሀብት ማጋዝ ሥራዬ ብሎ ተያይዞታል። እግዜር የለሹ የደርግ መንግሥት ወንበዴ የሚል ስም የሰጠው ለዝርፊያ ያለውን መቋመጥ ስለታዘበው ይሆናል። አሁን ምድራችን በዝርፊያ የታምሰች ናት። እናት አገራችንን ብንወዳትም፣ በሰፈነባት እንደ ባህል እየተገነባ ባለው ሌብነትና ዝርፊያ እናፍራለን። ሌባ እናት በሰረቀች ቁጥር ልጆቿ ይሸማቀቃሉ፣አንገታቸውንም ይደፋሉ።
ነቢያት ስለ ኢኮኖሚው እድገት ይናገራሉ። መጻሕፍትም እየተጻፉ ናቸው። በየመድረኩ የምንሰማው ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ይባርካታል የሚል ነው። አንዳንዶቹ ሌሎች የሚሉትን ሰምተው እንጂ በእርግጥም እግዚአብሔር ተናግአቸው አይደለም። በአገራችን የምንሰማው ትንቢት አብዛኛው የነቢያቶቹ የግል ምኞታቸው ነው እንጂ እግዚአብሔር የሚሰጣቸው መልእክት አይደለም። ምኞትና መልእክት ይለያያል።
3ኛ. ውሸትና ማታለል፡
መንግሥታችን ልማታዊ ነኝ ይላል ግን አይደለም። ዴሞክራት ነኝ ቢልም ዴሞክራሲው የማስመሰል፣የፖለቲካ ሽፋን ለማግኘት ሲል የሚያደርገው የቃላት ቅመማ ነው። በአገራችን ኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ቢኖርም ያ ሕገ መንግሥት የበላይ አይደለም። በአንድ ቀን ጉቦ ሊናድ የሚችል በአሸዋ ላይ እንደተሠራ ቤት ነው። እውነት እንነጋገር ካልን በአገራችን ላይ የመሪዎችና የካድሬዎች የበላይነት እንጂ የሕግ የበላይነት የለም። የኢሀአዴግ መንግሥት የሕገ መንግሥቱን ሥርዓት በሃይል ለመናድ የሚሹ ኃይሎች እያለ በሌሎች ላይ የሚፈረድ ቢሆንም ውሸትን እውነት አስመስሎ በመናገር የኢትዮጵያ መሪዎችን የሚያክል የለም። አንዱ ጄኔራል ሲናገሩ፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር የወያኔን ሠራዊት ይወደዋል ያፈቅረዋል ማለታቸው ብቻውን ለዚህ ማሳያ ነው። ክ1997 ምርጫ ጋር በተያያዘ በተነሳው ረብሻ በመንግሥት ታጣቂዎች የተገደሉ ስዎች ጉዳይ ሲነሳ የመንግሥት ባልሥልጣናት መልስ ሲሰጡ ሰዎቹ የሞቱት ባንክ ሲዘርፉ ነው ማለታቸው ሌላው ማሳያ ነው። አፈሩን ገለባ ያርግላቸውና የሞቱ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ደመወዛቸው ስድስት ሺህ ብር ብቻ ስለሆነ ባለቤታቸው ያንን እንደምንም አብቃቅተው እንደሚኖሩና በዓለም ላይ የመጨረሻ ዝቅተኛ ገቢ ያለው ሰው ማነው ቢባል እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸውን መስማታችን እንደ ተጨማሪ ማሳያ እንውሰድ። በምዕራቡ በኩል መሬት ለሱዳን ሊሰጥ የኢትዮጵያ መንግሥት እየተፈራረመ ያለው ለምንድነው ሲባል ለሱዳን ምንም መሬት አልተሰጠም፣ አንድም የኢትዮጵያ ገበሬ ከቦታው አልተፈናቀለም ማለቱ ሌላው ተጨማሪ ማሳያ ነው። መንግሥታችን ይህን ሁሉ እያለ መሬቱን ግን አሳልፎ እያሰጠ ነበር። ቴሌቭዝኑና ራዲዮ ቢሆን የኢህአዴግ መንግሥት ልሳን ስለሆነ እውነት ተናገረ ቢባል ሰዓት ብቻ ነው። ፖለቲካ በራሱ የቆሸሸ ጨዋታ ቢሆንም አሁን አመራር ላይ ያለውን መንግሥት ተከትሎ ወደ አገራችን የገባው የውሸት መንፈስ ግን የትም የሌለ ነው።
4ኛ. ሰብአዊ መብት ረገጣ
በዓለም አቀፍ ደረጃ የታውቁ የሰብአዊ ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን የመብት ረገጣ መስማት እጅግ የሚዘገንን ነው። በተለይም ከብሔራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሠራዊት በሚወስደው ከመጠን በሚያልፍ እምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹህ ዜጎች ሕይወት ይቀጠፋል። የኢህአዴግ መንግሥት ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ ወዲህ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር መገመት ከሚቻለው በላይ ነው። በሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ወቅት ብቻ ሕይወት የመንግሥት ታጣቂዎች በወሰዱት ተመጣጣኝ ባልሆነ የግፍ ርምጃ ክ500 በላይ ንጹሐን ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል። አምኔስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት እንደሚገልጸው ከ2015( እ ኤ አ) ጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ 800 ስዎች ተገድሏል። ከዚህም በተጨማሪ መንግሥት አስታጥቆ በሕብረተሰቡ ውስጥ ያሰማራቸው ሠራዊት በንጹሐን ላይ የሚያደርሱት ከመጠን ያለፈ ጥቃት ዓለምን ሁሉ ያንገሸገሸ ነው። ምንም የፖለቲካ አቋም የሌላቸውንም ጨምሮ ያለ ፍርድ ቤት ውሳኔ ያለ ጠያቂ በእሥር ማጎር፣ ማሰቃየት፣ መገረፍ ፣ስብዕናን የሚያዋርዱ ቅጣቶችን ማድረስ ፣ ያሉበት እንዳይታወቅ ማደረግ ወዘተ ይገኙበታል። አሁን ያለ የአገራችን ስብአዊ መብት ረገጣ በየትኛውም ዘመናትና አገዛዝ ያልነበረ መሆኑ ግልጽ ነው።
ይህ በሽታ እየሰፋና መጠኑን እየጨመረ መሄዱ በሁሉም ዘንድ የታወቀ ነው። ይህቺን አገር ከዚህ ችግር የሚያላቅቃት መፍትሔ ፣ የበሽታዋም መድኃኒት ከየት ይመጣ? ከተባበሩት መንግሥታት? ከልዕለ ኃያሏ አሜሪካ? ከአፍሪካ ሕብረት? ወይስ ከአውሮፓ ህብረት? ኢትዮጵያን ለመፍትሔ ፍለጋ በአሜሪካን አገር ከጮኹ፣ መንገድ አጣብበው ኡኡታና እሪታ ካበዙ ዘመን የለውም። አሁን አሁን እሱም ተከልክሏል ወይ እነርሱ ስልችቶአቸው ተውት መሰለኝ ጋብ ብሏል። በሰማይ ንጉሥ በእግዚአብሔር እጅ ግን መፍትሔ አለ። እርሱ በሰዎች ልጆች መንግሥት የሚሰለጥን ነው። ምድራችሁን እፈውሳለሁ ያለው እርሱ ስለሆነ መፍትሔና መላ ፍለጋ በእርሱ ደጅ እሪ እንበል፣ ኡኡታም እናሰማ። እርሱ ምድራችንን የፈውሳታል ፣ ለገዥዎቻችንም ልቦና ይሰጣቸዋል፣ የሕዝባችን እምባና የግፍ የሚፈሰው ደም ያበቃል። የአገራችን ጉዳይ ፈውስ የሚያስፈልገው ሕመም በመሆኑ ለመድኃኒትጥ ፍለጋ መሮጥ አለብን። መድኃኒቱ በጦርነት አይገኝም፣የሃያላን አገሮች ቢሮ በር ላይ ተሰባስበው እሪታ በማሰማትም አይገኝም። መድሓኒቱ እንዲገኝ በፍጹም ልብ ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ፊቱን ስንፈልግ ብቻ ነው። የአገራችን ፈውስ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ ከሌላ ቦታ ከየትም አይመጣምና። እግዚአብሔር አገራችንን የጐሳ ፖለቲካ፣ ሥርቆትና ዝርፊያ፣ውሸትና ማታለል እና ሰብአዊ መብት ረገጣ ከተባሉት ሥር የሰደዱ በሽታዎች አገራችንን ይፈውሳት! አሜን እንበል።