Tuesday, April 14, 2015

የቅዱሳን ልብ የሚያርፍበት አገልግሎት

የቅዱሳን ልብ የሚያርፍበት አገልግሎት
በአንድ ወቅት በአሜሪካን አገር ግራንድ ራፒዲስ በሚባለው ከተማ ጥቂት ኢትዮጵያውያን የእግዚአብሔርን ፊት በጾምና በጸሎት እየፈለግን ባለበት ሰዓት የእግዚአብሔርን ቃል እንዲያካፍል የተመረጠው ሰው ለመልእክቱ መግቢያ ያደረገውን የማይረሳ ምሳሌ ሁል ጊዜ አስታውሳለሁ፡፡ እንዲሀ ነው ነገሩ እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2009 የተባበሩት መንግታት የኢኮኖሚ ፎረም ባደረገው ዓመታዊ ስብሰባ የተለያዩ የመንግሥታቱ አባል አገሮች ተወካዮች የየአገራቸውን የሥራ ሪፖርት ይዘው ቀረቡ፡፡ ከየአገሩ የመጡ ወካዮች ምን ለሥራት ታሰቦ ምን አንደተከናወነና እንዴት ያለ ለውጥ እየታየበት እንደሆነ እያካፈሉ አንዳቸው ከሌላው ልምድም እየቀሰሙ ባለበት ወቀት የአንድ አገር ሪፖርት ግን የብዙዎችን ልብ የነካና የተደነቀ ሆነ፡፡ ያቺ አገር በሩቅ ምሥራቅ የምትገኝ ባርማ በመባል የምትተወቅ አገር  ናት ፡፡ ባርማ በ2009 .ም ልትሠራ ያቀደችውና ያከናወነችው ሌሎች አገሮች ካቀረቡት ጋር በፍፁም የይገናኝ ነገር ግን ሁሉንም ያስደነቀ አቀራረብ ነበር፡፡ ሌሎች  ስለ ልማት፣ ስለ አኮኖሚያዊ እድገት፣ ስለ ውጭ ግንኙነትና ስለ ወታደራዊ ዝግጅቶቻቸው ሆኖ ካቀዱት ምን ያህል እንደተሳካላቸው ነበር ያቀረቡት፡፡  ባርማ ግን በ2009 መግቢያ ላይ የያዘቺው እቅድ በአገሪቱ ውስጥ ያለ እያንዳንዱን ዜጋ በነፍሰ ወከፍ ደስተኛ እንዲሆን ስለማድረግ ነበር፡፡ ከልማት ሥራዎች ሁሉ የሚቀድመው የዜጋው ረክቶና ተደስቶ የመኖር ጉዳይ ስለሆነ ከዚህ አንፃር አቅዳ 90 በመቶ እደተሳካለት ያቀረበቺው ሪፖርት ሁሉንም የጉባኤ ተሳታፊዎችን ሊያስደንቅ ችሏል፡፡
ይህ ለእኛ የእግዚአብርን ሕዝብ ምናገለግል ሰዎች እጅግ በጣም አስገራሚ ትምህርት ያለበት ምሳሌያዊ መልእክት ነው፡፡ እኛ ከባርማ መንግሥት ይልቅ የምናገለግላቸውን ቅዱሳን ልባቸው እንዲያርፍ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ እግዚአብርም እኛን በዚህ ምድር ይ ያስቀመጠን የእርሱን አሳብ እያገለገልን በስሙ የተጠሩትን ሁሉ እንድናንፃቸው ነው፡፡ የአገልጋዮች አገልግሎት የምዕመናንን ልብ የሚያሳፈርፍ እዲሆን ደግሞ የእግዚዘአብር ቃል ይመክረናል፡፡ አገልግሎታችን የቅዱሳንን ልብ እንዴት ማሳረፍ እንደሚቻል ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልሞና ጻፈውን መልእክት ከቁጥር 1-7 መመልከት እንችላለን፡፡ ወደ ዋናው አሳባችን ከመግባታችን በፊት ስለ ፊልሞና መጽሐፍ ሁለት ወይም ሦስት መሰረታዊ በሕሪያቶችን እንመልከት፡፡ የፊልሞና መጽሐፍ ዋሪያው ጳውሎስ እሥር ቤት ሆኖ ከጸፋቸው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ ጳውሎስ ይህንን መፅሐፍ በሚጽፍበት ወቅት በሮም እሥር ቤት ሊሆን ይችላል፣ ወይም በሌላ ቦታ ሊሆን ይችላል ብቻ መልእክቱን ያስተላፈው ከእሥር ቤት ነው፡፡ የፊልሞናን መጽሐፍ በጣም ተናፋቂ ከሚያደርጉት ነገሮችም አንዱ ይህ ነው፡፡ ከየትና እንዴት በማንስ ተጻፈ የሚለው አሳብ የሚተላለፈው መልእክት ተሰሚነት እንዲኖረውና አቅምም አንዲያገኝ ያደርገዋል( .9)፡፡ ሁለተኛው የፊልሞና በጣም አጠር ካሉ ወይም ምዕራፍ ከሌላቸው መጻሕፍት ይመደባል፡፡ በጠቅላላው በመጽሐፍ ቅዱ ውስጥ ወደ አራት ያህል መጻሕፍት በምዕራፍ ያተከፈሉ ሲሆን እነርሱም ብዲዩ፣2ኛ ዮሐንስ፣ 3ኛ ዮሐንስ ና ፊልሞና ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በምዕራፍ አይከፋፈሉ እንጂ ትልቅ ቁም ነገር ያዘሉ ናቸው፡፡ በምዕራፍ ያልተከፈሉበት ምክንያት አጠር ባለ መልክ ስለቀረቡ ብቻ እንጂ መልእክቱ ከእግዚአብሔር ስላልሆነ አይደለም፡፡ ሦስተኛ የፊልሞናን መጽሐፍ ልዩ የሚያደርገው የመልእክታቴ ምጋቤ አካል ከሆኑት መጸሕፍት የሚመደብ መሆኑ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ለቡድን ወይም ከቤተ ክርስቲያን ወይም ለአንድ አገልግሎት ክፍል የተላከ ሳይሆን የሕዝብ እረኛና አገልጋይ ለሆነ ሰው በግሉ የተላከ የመጋቢያዊ መልእክት ያዘለ ነው፡፡ ለአንድ ግለሰብ የተላኩ ሌሎችም ጻሕፍት በአዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉ ሲሆን ሁላቸውም የየራሳቸው ባሕሪያት ያሉአቸው ናቸው፡፡
በዚህ አጭር ትምህርት ውስጥ ሐዋሪያው ጳውሎስ ለፊልሞ የሚያቀበውን መልእክት ሁሉንም ማየት እችልም ፣ ነገር ግን ከቁ 1-7 ያለውን ብቻ እንመለከታን፡፡ ይንን መልእክት የሚያስተላልፈው የእግዚአብሔር ሰው ጳውሎስ የጌታ አገልጋይ ከሆነው ከፊልሞና ጋር ትልቅ የአልግሎት መተሣሠር ነበራቸው፡፡ ጳውሎስ በእሥር ቤት ሆኖ ስለ ፊልሞና አገልግሎት የሰማው ነገር በእርሱ ላይ የፈጠረው አዎንታዊ ተጽእኖ በዚህ የንባብ ክፍል ውሰጥ ይገኛል፣ ምክንያቱም ጳውሎስ በፊልሞና አገልግሎት ምክንያት መጽናናቱንና መደሰቱን ይናራል( . 7)፡፡ በፊልሞና አገልግሎት በቤተ ክርሰቲን ያሉ ቅዱሳን ልብ በማረፉ ምክንያት ጳውሎስ ተደስቷል፣ በብዙ መጽናናት ተጽናንቷል፡፡ እንዲህ ያለ አገልግሎት ማገልገል እንዴት ዓይነት መታደል ነው!
ፊልሞና የሚያገለግለው አገልግሎትና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያደርገው ሥራና ተግባር ሁሉ የሕዝቡን ልብ ከመረበሽና መንፈሳቸውን ከማናወጥ ይልቅ ልባቸውን የሚያሳርፍ ነበር፡፡ ስለዚህ እኛ ዛሬ በዚህ ዘመን የምንገኝ አማኞች የቅዱሳንን ልብ ከማሳረፍ አንፃር እንዴት አይነት አገልግሎት እየሰጠን እንደሆነ ራሳችንን መመልከት ይኖርብናል፡፡ እስቲ የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፍ ሕይወትና አገልግሎት ምን እንደሚመስል ሐዋሪያው ጳውሎስ ለፊልሞና ከጻፈው መልእክት እንመልከት፡፡
1. አገልገሎቱ የቅዱሳንን ልብ ሚያሳርፈው አገልይ የይቅርታ ልብ ያለው ነው፡፡
ጳውሎስ ይህንን መልእክት ለፊልሞና የሚልክበት ተቀዳሚ ምክንያት በፊልሞናና በአናሲሞስ መካከል ክርስትያናዊ ይቅርታን ለማስፈን ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ሙሉውን የሚገረው ስለ ይቅርታ ነው፡፡ ፊልሞና በፍቅርና ሌሎች መልካም ሥራዎች የቅዱሳንን ልብ ያሳረፈ ምርጥ አገልጋይ ቢሆንም ጳውሎስ በድጋሚ ስለ አናሲሞስ ይጠይቀዋል፡፡ አናሲሞስ የፈልሞና አገልጋይ (በጥንት አባባል ባሪያው) ሆኖ ከፊልሞናም ጋር አብሮ ይኖር ነበር፡፡ ነገር ግን በአንድ ወቅት ፊልሞናን ዘርፎ በመኮብለሉ የፊልሞና ልብ በአናሲሞስ አዘነ፡፡ ይሁን እንጂ አናሲሞስ ኮብልሎ በሄደበት ጳውሎስ አገኘውና ወንጌል ሰበከለት፣ አናሲሞስም  በጌታ በኢየሱስ አመነ፡፡ ጳውሎስ በእሥር ቤት በነበረበት ወቅት በወንጌል ንዲያምን ምክንያት ስለሆነው አናሲሞስ ይረዳና ያግዘው ነበር፡፡ በዚህን ጊዜ የአናሲሞስ ለጳውሎስ አስፈላጊ ሰው ቢሆንም ያለ ፊልሞና ፈቃድ ለራሱ ሊያስቀረው ስላልፈለገና በሁለቱ መካከል የይቅር መንፈስ እንዲሰፍን ስለፈለገ ወደ ፊልሞና ይልከዋል፡፡ እንዲያውም ፊልሞና አናሲሞስን እንደ ወንድሙ እንዲቀበለው ይማጸነዋል፡፡ ያ ብቻ ሳይሆን የተደበለውንም ሁሉ በእርሱ ላይ እንዲቆጥርበት ይጠይቀዋል፡፡ እንግዲህ ከዚህ የምናየው እርቅና ሰላም በሌለበት ሥፍራ ሁሉ ጭንቀትና መረበሽ እንዲሁም አለመረጋጋት መኖሩን ነው፡፡ ስለዚህ ነው ሐዋሪያው እባክህ ልቤን አሳርፍልኝ የሚለው! ይህ የጌታ አገልጋይ ባደረጋቸው ሥራዎች ሁሉ የቅዱሳንን ልብ በማሳረፍ የሚታወቅ ቢሆንም አሁን ደግሞ ለአናሲሞስ ይቅርታ በማድረግ የበለጠ የጳውሎስንና የሌሎችን ልብ እንዲያሳርፍ ተጠይቋል፡፡ ይቅርታ ሲደረግ የቅዱሳን ልብ ያርፋል ማለት ነው፡፡ ሁለት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሲጫቃጨቁና ሲቃረኑ እንቅልፉን የሚያጣው ምዕመኑ ነው፡፡ ሁለት መጋቢዎች ባለመግባባት እርስ በእርሳቸው ሲገፋፉ የሚያዝነውና የሚረበሸው ጉባኤው ነው፡፡ መሪዎች እርስ በእርሳቸው የሰላምና የፍቅርን አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት በምዕመናን መካከል ያለው ደስታና ፍንደቃ ትልቅ ይሆናል፡፡
የብሉይ ኪዳን መጸሕፍትን በምንመለከትበት ወቅት የእሥራኤል ሕዝብ ለጦርነት ከተጋለጠባቸው ምክንያች አንዱ የመሪዎች ሁኔታ ነው፡፡ በአናጸሩ ደግሞ አገርን ከሚመሩ ነገሥታት የተነሳ ምድርት አርፋ እንደምትቀመጥ የእግዚአብሔር ቃል በእርሱ ጊዜ ምድሪቱ በሰላም አርፋ ተቀመጠች እያለ ይናገራል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ በቤተ ክርስቲያንም የሚያገልግሉ መሪዎች እርስ በርሳቸው በፍቅር ሲቀባበሉና ሲዋደዱ በመላ ቤተ ክርስቲያን የሚታየው ደስታ እጅግ የላቀ ይሆናል፡፡  ጳውሎስም ፊልሞናን ልቤን አሳርፍልኝ  ማለትም ይቅርታ በማድረግ ልብ የሚያሳርፍ ሥራህን ቀጥል የሚለው ለዚህ ነው፡፡
ዛሬም እኛ የሚያስፈልገን የአገልግሎት ብዛት አይደለም፡፡ ብዙ መስበክም አይደለም፡፡ ነገር ግን የቅዱሳንን ሁሉ ልብ የሚያሳርፍ አገልጋይ ሆነን መገኘት ነው፡፡ እኛ ይቅርታን የማይቀበል በቀለኛ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ያደግን ሰዎች ነን፡፡ አብዛኛው ባህላችን ቁጣና በቀል የተሞላ ነው፡፡ ብድር በምድር የሚለው አስተሳሰብ አብሮት ከማደጉ የተነሳ  ትውልዳችን ይቅርታን መጠየቅን እንደ ሽንፈት፣ ይቅርታን ማድረግን እንደ ሞኝነት የሚቆጥር ነው፡፡  ጌታን ተቀብለን አገልጋዮችና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ከሆንንም በኃላ እንኳ ያ አብሮን ያደገው ልማዳችን ከውስጣችን አልወጣ ብሎ ጊዜ ይወስድብናል፡፡ ስለዚህ ብዙዎቻችን በእግዚአብሔር ቤት እንበቃቀላለን፣ አንዳችን ሌሎችን እናሳድዳለን፡፡ በተለያየ የአገልግሎት ዘርፎች ብናገለግልም በእግዚአብሔር መድረክ ላይ እያለንም በቀለኝነት ያጠቃናል፡፡ ይህ ከመሆኑ የተነሳ የእግዚአብሄርም ልብ አልተደሰተም የቅዱሳንም ልብ አላረፈም፡፡ እኛ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እያሳረፍን ነው ወይስ እያሳዘንን; እያራወጥነው ወይስ እያረጋጋነው፣ እያጽናናነው ወይስ እያስጨነቅነው ነው የሚለውን ጠይቀን መልስ ማግኘት ይኖርብናል፡፡ የእግዚብሄርን ቃል በማስተማርና የተያዩ ቅዱሳት መጻሕፍትን መበጻፍ በዘመናችን ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ትልቅ አክብሮት ያላቸው ዶር ጆን ማካርተር ይቅርታ አለማድረግ እንዴት ያለ ክፉ ነገር እንደሆነ እንደሚከተለው ገልተዋል፡፡
ይቅርታን አለማድረግ ባለፈው የመራርነት ሕይወት እሥረኞች አንድንሆን የሚያደርገን ነው፡፡ ይቅርታን አለማድረግ ለሰይጣን አሠራር የተከፈተ በር የሚሰጥ ሲሆን እኛም አጋንንትን በዚያው እንኳን ደህና መጣህ እያልነው ነው፡፡ ይቅርታ አለማድረግ በእኛና በእግዚአብሔር መካካል ላለን ሕብረት እንቅፋት ነው፡፡ ምከንያቱም ጌታ ኢየሱስ ሲያስተምር ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ የሰማዩ አባታችሁ ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡ ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ካላልን ደስታችንና ሰላማችን ይወሰድብናል፡፡ ጳውሎስ በፊልሞናና በአናሲሞስ መካካል ሆኖ ሁለቱን የሚሸ መግላቸው ይመስላል፡፡ አናሲሞስ ፊልሞናን በጣም አድርጎ በድሎታል፡፡ ጳውሎስና ፊልሞና በነበሩበት ዘመን አናሲሞስ ያደረገውን ዓይነት በደል የፈጸመ በባህላቸው መሠረት ይወገዛል ፣ ይወገራል፣ ይሰደዳል እንዲያውም ገደላልም፡፡ እርሱ የፈጸመው ወንጀል በማንኛውም ማኅበራዊና ሕዝባዊ ጉዳዮች ሥፍራ እንዳይኖረው የሚያደርግ ነው፡፡ምክንያቱም አናሲሞስ ለፊልሞና ባሪያው ሆኖ እያለ ያንን በአሠሪዎች ዘንድ ከባድ ወንጀል ሆኖ የሚታወቀውን ጥፋት ሠራ፡፡ ምናልባት አናሲሞስ ከአካባቢው የሸሸው የሚደርስበትን ቅጣት ፈርቶም ሊሆን ይችላል፡፡ የእግዚአብሔር ሕግ ግን ይህንን በደለኛውን ሰው አንደ ወንድምህ ቁጠረው ይላል፡፡ ይህ ቀላል ሊሆን የማይችልበት ምክንያት አለ፡፡ አንደኛ ባሪያና ጌታ ሁለቱ እኩል በማዕድ መቀመጥ የሚችሉበት ባህላዊ አግባብ በጊዜው አልነበረም፡፡ ዘራፊና ቀመኛ ምንም ቢሆን ከተቀማው ሰው ጋረ ሕብረት እንዲያደርግና ከዚያም አልፎ እንደ ወንድም ሊቀበል የሚችል ሥርዓትም ሆነ ልማድ አልነበረም፡፡ የእግዚአብሔር ህግ ግን ከዚህ ሁሉ ይለያል፡፡ እንደ ወንድምህ ቁጠረው ፣ ባሪያ ከነበረበት እንደ ወንድምህ አድርገው የሚል ነው፡፡ ጥፋት አድርሶ የኮበለለውን የጠገበ ሠራተኛ ወደ ሥራው አንዲመለስ አሠሪውን እንማፀነው ይሆናል ፣ ወንድም አድርገው ለማለት ምንም የማይታሰብ ነው፣ ማለት የሚፈልግም ካለ ደግሞ ሆን ብሎ ሽምግልናውን ለማደፍረስ እንደሚፈልግ ሰው ለፈረጅበት ሁል ይችላል፡፡ ጳውሎስ ለፍልሞና የሚናረው መልእክት ግን ወደ ሥራው እንዲመለስ ከሚለው የዘለለና እንደ ወንድም ቁጠረው የሚለው ነው፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ክርስትና ሲገባን ብቻ ነው፡፡ ስለ ይቅርታ ሰብከው ሲመለሱ ወንድማቸውን ይቅር አልልም ብለው ሳምንት ሙሉ ሽማግሌ የሚያመላልሱ አገልጋዮች ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ ስብከት ችለዋል እንጂ ክርሰትናው ገና አልገባቸውም አሊያም ክርስትና የሚያሰከፍለውን ዋጋ ገና አላወቁትም፡፡ ምክንያቱም ክርስትና የዘረፈህን ጥጋበኛና ጎረምሳ አገልጋይን ወደ አንተ ሲመጣ እንደ ወንድምህ አድርገው እንጂ እንደ ሠራተኛህ አትየው የሚል ነው፡፡
ጳውሎስ ስለ ፊልሞና የተረዳው ሁሉ አዎንታዊ ነው፡፡ የሚያርምበት አንድም ነገር እስከማይኖርበት ድረስ ሕይወቱ የተመሰከረለት ሰው ነው፡፡ ምን አይነት ባሕሪያ ነው! አሁን ግን ለአናሲሞስ ይቅርታ በማድረግ የበለጠ ይምሰገናል ክርሰቲያናዊ ጀግና ይባላል ወይም ብዙ የሆነው መልካም ነገሩ በአንድ ነገር ምክንያ ብቻ ዋጋው ሊረክሲበት ይችላል፣ ያውም ይቅርታ በማድረግ ወይም ባለማድረግ፡፡ ብዙ የመድረክ ጀግኖች ተፈትነው በቀላሉ ክብደታቸው ታወቀ፡፡ እኔ እኮ ጌታን ካገኘውና በመንፈስ ቅዱስ ከተሞላው ይህን ያህል ሰዓት ሆኖኛል፣ እነ እገሌም በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉት እኔ እጅ ጭኜ ስጸልይ ነው ብለው የሰውን ሁሉ እትኩሮት ሲስቡ የኖሩ ቱባዎቻችን ክርስትናቸው ከወጣበት በአንዴ ሲወርድ ያየነው ለባልንጀራቸው ይቅርታ እንዲያደርጉ ሲጠየቁ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ ያየን ቀን ነው፡፡
2. የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፍ አገልጋይ ስለ ሰዎች ሕይወት የሚጨነቅ ነው( .4)፡፡
ፊልሞና ለሰዎች ግድ የሚለው ለእርሱ የሚጨነቅበቅዱሳን ሁሉ ዘንድ ፍቅር ያለው ሰው ነበር፡፡ እር ከተወሰኑ ሰዎች ጋር በፍቅር የተሳሰረ ፣ ከተቀሩት ጋር ደግሞ አኩራፊ ዓይነት ሰው ሳይሆን ከቅዱሳን ሁሉ ጋር በፍቅር የሚኖር ሰው ነው፡፡ ይህ ፍቅር ደግሞ ለሰዎች ሁሉ ሸክም እንዲኖረው አድርጎታል፡፡ ጳውሎስ ለፍልሞና ፍቅር እንደነበረው ከቁ.11-14 ያሳየናል፡፡ አናሲሞስ በእሥር ቤት ላለው ለጳውበጣም ስለሚያስፈልገው ከራሱ ጋር ቢያቆየው የማይወቀስበት ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ አንደኛው፣ አናሲሞስ ገና ጌታን ሳያገኝ ከፊልሞና ኮብልሎ ሄዷል፡፡ ሁለተኛ ወንጌል መስክሮ  እንዲለወጥ ምክንያት ስለሆነው አሁን የወንጌል ልጁ ሆኖታል፡፡ ስለዚህ ቢያስቀረው ፊልሞናም ቢሆን ቅር ሊሰኝበት አይችልም፡፡ ይንጂ ጳውሎስ ከራሱ ጥቅም ይልቅ የፍሞናን በመስቀደም አናሲሞስን ወደ ፊልሞና ላከው፡፡ ለእኔ ይልቅ የአንተ ይሻላል የሚል አቅም ያለው ክርስትና ያለው ሰው ነው፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔም ደስ የሚሰኝበትና የቅዱሳን ልብ የሚያርፍበት ሕይወት እንዲህ ዓይነቱ ነው፡
3. የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፍ አገልጋይ ስለ እግዚአብሔር የሚያስብ ነው(4-5)፡፡
የእግዚአብሔር ክብርና ከእርሱ ጋር ያለን ሕብረት ግድ የሚለን ስንሆን የቅዱሳን ልብ ያርፋል፡፡ ጳውሎስ በዚህ ክፍል ስለ ፍልሞና እምነት ሰምቶ እግዚእብሔርን ያመሰግናል፡፡እምነት ሙ በሙሉ ለእግዚአብሔር ያንን መሰጠት መተማመን እንዲሁም በጌታችን በፍጹም ማረፋችንን የሚያመለክት ሲሆን እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ያገናኘናል፡፡ ፍቅር ደግ ከሰዎች ጋር ያገናኘናል፡፡ ፡ ፈልምና እነተኛ የሆነ እምነት የነበርውነና በእውነትም የተመሰከረለትም አማኝ ነው፡፡ ሰዎች ከወንድሞቻቸው ጋር ያላቸውን ነገር የሚያላሹት ከእግዚአብሔር ጋራ ያላቸው ነገር መበላሸት ሲጀምር ነው፡፡ ብዙዎች ከእግዚአብሔርና ከወንድሞቻቸው ጋር ካላቸው ህብረት ይልቅ ለመድረካቸውና ለአገልጋይነት ስማቸው ትኩረት ይሰጣ፡፡ ከአሥር ዓመት በፊት ከአዲስ አባባ 400 ኪሎ ሜትር አካባቢ የምትገኝ አንዲት ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጀቺው ኮንፍራንስ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስበክ ሄድኩ፡፡ ጉባኤው በጣም ትልቅ በመሆኑ ጸሎት ቤቱ ስላልቻለ ፕሮግርሙ የተካሄደው በሜዳ ላይ ነበር፡፡ በዚያ ኮንፍራንስ መልእክት ካቀረብኩ በኋላ የንሰሐ ጥሪ ሳቀርብ አንድ ወጣት ሚስቱን እንደበደላትና ይቅርታ ሊጠይቃት እንደሚፈልግ ተናገረ፡፡ ስለዚህ ከቤተ ክርስቲያን መጋቢ ጋር በመሆን ሚስቱን አስጠራናትና ይቅርታ እንድታደርግለት ስንጠይቃት አባቴ ይህንን መስማት አለበት አለች፡፡ አባቷ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ ስለሆነ ከሰዎች ጋር የነገውን ፕሮግራም በሚመለከት አንዳንድ ሥራዎችን እየሠራ ካለበት አስጠራነውና ጉዳዩን ሁሉ አጫወትነው፡፡ ልጅቷ ይቅርታ አድርጋ ወደ ትዳሯ የመመለስ ልብ ቢኖትም የአባቷ አቋም ግን ከጠበቅነው በላይ አስቸጋሪ ሆኖ ተገኘ፡፡ ልጅቱ ከባሏ ጋር በተፈጠረው ጊዜየያዊ አለመግባባት ምክንያ ካለችበት ትዳር ወጥታ ወደ አባቷ ቤት መታ እዛው ናት፡፡ ጉዳዩን ለማስተካካል በጣም ሰፊ ጊዜ ወሰደብን፡፡ ልጁን የበደለውን ሰው ይቅር እንዲል ደጋመን ብንለምነውና ብማጸነው አባትዬው በጭራሽ እምቢ አለ፡፡ በመጨረሻም ላይ እንዲህ ኣይነት ክርስቲና ይዘህ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ ትሆን ስለማትችል አግደንሃል ሲሉት እንደዚህ ከሆነ እሺ እንዳላችሁት ይሁን አለ፡፡ ወጣቱ ባለትዳር ሚስቱን የዞ ቤቱ ቢገባም ይህ ሽማግሌ ስለ ክርስቲናውና እግዚአብሔር ስለሚጠብቅበት ኑሮ ሳይሆን የተጨነቀው ስለ ሽምግልናው መሆኑ የሁላቸንንም ልብ እንዳሳዘነ አስታውሳሁ፡፡
ዛሬም በእኛ ዘመን ስለ ስማቸውና ስለ መድረካቸው እንዲሁም በሰው ፊት ስለሚታየው አገልግሎታቸው እንጂ ስለማይታየው መንፈሳዊ ሕይወታቸውና የጌታ መንፈስ ከእነርሱ ስለሚፈልግባቸው ሕይወታቸው ግድ የማይላቸው ብዙ አገልጋዮችና መሪዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ፊልሞና ግን እንዲህ ዓይነት ሰው አይደለም፡፡ የሰሙትን ሁሉ የሚያስመሰግን እምነት ያለው ሰው ነው፡፡ አንዲህ ዓይነቱ ሕይወት እግዚአብሔርን ያስደስዋል ፣ የቅዱሳንንም ልብ ያሳርፋል፡፡
4. የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፈው ስለ እውነተኛ ሕብረት የሚያሳስበው ነው፡( 6)፡፡
በጌታ ያለን አማኞች ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር እውነተኛ እምነትን የቅዱሳን ሕብረት እንደሚከተለው ነው፡፡ አንድነት፣የወንድማዊ ፍቅርና ሰላም የክርስትያንነታችን ምልክትና የሕይወታችን ክፍል ነው፡፡ ከሌሎች ጋር በምናሳልፍበት ወቅት ከሌሎች እንማራለን፣ እንታነጽባቸዋለንም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን የምንሄደው ስብከት ሰምተንና ተነቃቅትን ለመመለስ ብቻ ከሆነ ያ ሁኔታ እኛን ራስ ወዳዶች ያደርገናል፡፡ ይልቁንም ለሌሎች በረከት ለመሆን፣ ከእርሱም ጋር ለመተያየትና እርስ በእርሳችንም ለመልካም ሥራ እንድነነቃቃ ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት የምንሄደው ለጋራ በረከት ነው፡፡ የወንድማችንን ሐዘን ሀዘናችን ደስታውንም ደስታችን ልናደርግ ነው ፡፡ የእኛንም ሸክም እነርሱ እንዲጋሩ ለማድረግ ጭምር እንጂ ተሰብከን፣ ወይም ሰብከን ወይም ዘምረን ወይም ለራሳችን በረከቱን አፍሰን ልንመጣ ብቻ አይደለም፡፡ ቅዱሳን ልብ የሚያርፈው ግን አንዳችን ከሌላው ጋር በሕብረት ስንተሳሰር ነው፡፡ በርካታ አገልጋዮች ሰዎች ሲጣሉ ደስ ይላቸዋል፡፡ እንዲያው ሰው ምን ይለናል ብለው እንጂ ዱላ ቢያቀብሉ የማይጠሉ አናካሾች አይጠፉም፡፡አንዲት ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ አሁን ወደ እኛ ይመጣሉ ብለው የሚደሰቱ ቤተ ክርስያን አገልጋዮች ጥቂት አይደሉም፡፡ እነ ፊልሞና ግን ይህ አይነከካቸውም፡፡ ስለ ሕብረትና አንድነት የሚያስቡና የሚጨነቁ፣ የሚጠበቡም ናቸው፡፡ ስለዚህ እንደዚህ ባሉት አገልጋዮች ሕይወትና አገልግሎት የቅዱሳን ልብ ያርፋል፡፡
5. የቅዱሳን ልብ የሚያርፍበት አገልጋይ ስለ መንፈሳዊ እውቀት የሚያሳስበው ነው( 6)፡፡ እውቀት ስንል ተራ መረጃ ሳይሆን ስለ እግዚአብሔር ያን ጥልቅ መረዳት ማለታችን ነው፡፡ የእግዚአብሐሔርን ነገር በጽንሰ አሳብ ደረጃ ማወቅናTheoretical knowledge በሕይወት ልምምድ ውስጥ ገብተን ማወቅ /experiential knowledge/ ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ፅንሰ አሳብ በሆነው እውቀት ወደ ንስሐ አምልኮ፣ እንዲሁም ወደ ይቅርታ ሕይወት መድረስ አይቻልም፡፡ በአገራችን ሳለሁ በአውሮጳና በአሜሪካ እንዲሁም በሌሎች የምዕራብ አገሮች በየክረምቱ ስለሚወርደው በረዶ ከሚሰማው ነገር ተነስቼ ለሌሎችም ሰዎች አስረዳቸው ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የተቆረቆሩ የፕሮቴስታንት አማኞች ቤተ ክርስቲያን ሕንጸዎች ጣሪያቸው ከመሀል ከፍ ያለና ዳርና ዳሩ ዝቅ ያለ ሲሆን ይህ አሠራር ምዕራባውያን በረዶው ሲወርድ ጣሪያው ላይ ተከምሮ እንዳይጎዳው እየተንሸራተተ እንዲወርድ አድርገው ስለሚሠሩት ሚሲዮናውያኑ ወደ አገራችን ሲመጡ ያንን የለመዱትን ዓይነት ቤት ስለሚሠሩ ነው የጸሎት ቤቶቸችን ሕንጻዎች ከሌላው የተለዩ የሚሆኑት ሲባል ስለ ሰማሁ እኔም ለብዙዎች የሰማሁትን ያንኑን አስረዳ ነበር፡፡ ነገር ግን ያንን ሁሉ የማስረዳው በረዶውን በዓይኔ እንኳን ሳላየው ነበር፡፡ ከብዙ ጊዜያት በኋላ ወደ ሚቺጋን መጥቼ በረዶ ሲወርድ፣ ከተማውን ሁሉ ሲሸፍን፣ መንገዱን ሁሉ ሲዘጋ በቤቶች ሁሉ ጣሪያ ላይ ተከምሮ ከዚያ እየተንሸራተተ ሲወድቅ፣ መንገዱን ሁሉ ሸፍኖ ለመንዳት ሲያስቸግርና እያንዳንዱ የሚቺጋን ነዋሪ በወፋፈፍራም ልብሶች ተጀቡኖ ሲሄድ ሳይ ለበረዶ ያለኝ እውቀት የተለየ ሆነ፡፡ እንዲያውም እኔ በበረዶ ላይ ሲነዳና መኪናዬ መንገድ ስታ የወጣችበትን አጋጣሚ ሁሉ ሳስበው ሰው በመረጃ ብቻ የሚያውቀው እውቀት በሕይወት ልምድ ከሚያውቀው ምን ያህ የተለየ እንደሆነ በለጠ ተገነዘብኩ፡፡ ጳውሎስም ይህ የሕይወት ልምድ እውቀት እንዲበዛለት ለልሞና እንደሚጸልይለት ቃል ይገባለታል፡፡ ይህ ጥልቅ እውቀትና መረዳት አፓጎኒሲስ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ስለ እግዚአብሔርና በእኛ ውስጥ ስላለው መንፈሳዊ ነገር ጥልቅ የሆነ መረዳት a deep understanding about God and about what in us/ ማለታችን ነው፡፡ በእኛ ዘንድ እግዚአብሐየር ያቀመጠው በጣም ብዙ የሆነ መልካ ነገር አለ፡፡ ጌታ ኢየሱስን ካመንንበት ጊዜ ጀምሮ ከእርሱ በጣም ብዙ መንፈሳዊ ስጦታዎችን ተቀብለናል፡፡ ይህንን እግዚአብሔርን አውቆ መከተልና አውቆም ማገልገል ሕይወታችንን ያሳድገዋል፤ በእግዚአብሔርም ላይ ያለን መተማመን ይጨምራል፡፡ በእኛ ዘንድ ያው ሁሉ በማወቅ የሚው አሳብ ል ትኩረት የሚሰጠው ነው፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ብዙ መልካም ነገሮችን አስቀምጧል፡፡ ከጌታ ያገናቸው መንፈሳዊ ስጦታዎች ክርስቶስን ወደ ወቅ እንድንደርስ የሚያደርጉን ናቸው፡፡ ስለዚህ የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፍ አገልጋይ በክርስቶስ ስላው እውቀት ግድ የሚለው ነው፡፡
6. የቅዱሳንን ልብ የሚያሳርፍ አገልጋይ ለክርስቶስ ክብር ግድ የሚለው ነው፡፡
ፍልሞና ሁሉንም ነገር ያደረገው ለክርስቶስ ነው፡፡ መንፈሳዊ ፍሬንም የሚያፈራው ለክርስቶስ ነው፡፡ ጳውሎስ በአንተ ያለው ነገር ለክርስቶስ ፍሬን እንዲያፈራ እለምናለሁ በማለት ለፍልሞና የሚጸልየውን የጸሎት ይዘት ይገጻል፡፡ በአገልግሎታችን ፍሬን ብናፈራ ያ ፍሬ ክርስቶስን ለማክበር መሆን አለበት፡፡ ሰዎችንም በአገልግሎታችን የምናዘጋጀው ለክርስቶስ ነው፡፡ ክርስቶስ በእኛ ሕይወትና ኑሮ በሚከብርብት ወቅት የምናገልግላቸውና አብረውን ጌታን የሚያመልኩ ሰዎች ልባቸው ያረፈ ይሆናሉ፡፡
ስለዚህ ጳውሎስ ይንን አንቀጽ ሲደመድም ልቤን አሳርፍልኝ ይላል፡፡ ዛሬም ሰዎች ተንቀዋል፣ ፈርተዋ፣ተረብሸዋል፣ ግራም ተጋብቷል፣ምእናንም በአገልጋችና በመሪዎች መካከል ካለው አላስፈላጊ ሽኩቻ የተነሳ ተንገላትተዋል፣ ከቦታ ወደ ቦታ ተንከራተዋል፣ ከአንዱ አበባ ተነስታ በሌላው ላይ እንደምትቀመጥ ከዚያም ተነስታ ወደሌላው አበባ እንደምትበር ንብ ተጉላልተዋል ፡፡  በንፈሳዊ ሕይወታቸው መጠንከር አልቻሉም፡፡ አማኞች ሥር መስደድ ሲጀምሩ መሪዎችና መድረክ ናፋቂ ሰባኪዎች ካሉበት ሥፍራ ያፈናቅሉአቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሳ በመንፈሳዊ ሕይወት መጭብርብር ውስጥ ገብተዋል ፣አያሌዎችም ለአውሬ ተጋልጠዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን እኛ አገልጋዮች ስለ እነርሱ ግድ አላለንም፡፡ ስለዚህ ቆም ብለን በማሰብ የምዕመናኖቻችን ልብ ልናሳርፍ ይገባናል፡፡ ጳውሎስ ለፍልሞና የሚልከው ይህ መልእክት ለአገልጋች ሁል ማነቂያ ደወል ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ የቅዱሳንን ልብ ሚያሳርፈውን ማንነት እግዚአብሔር ይስጠን፡፡ አሜን፡፡








Thursday, April 9, 2015

የኢየሱስ ማኅተም
( የማንነታችን ምልክት )
                                                                                                                                     በፓስተር ሳሙኤል ሾንጋ
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በ1992 ..ገዳማ በምዕራቡ በአገራችን ክፍል አንድ በዓይነቱ የተለየ ወፍ ተገኘና መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶት ንደተንከባከበው ይታወቃል፡፡ ይህንን ወፍ ልዩ የሚያደርገው ነገር መልኩ ብቻ ሳይሆን በአንገቱ ላይ ንጠለጠለው ታግ ወይም ምንነቱን የሚያሳይ ጽሑፍና ቁጥር ያለበት ካርድ መኖሩ ነው፡፡ የካከቢ ጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማሩት ሰዎች ይህንን በያዩበት ወቅት ይህ ወፍ ከየት አካባቢ እንደመንዴትስ እንደመ ጥናት ድረግ ነበረባቸውና ሲጠና በታጉ ላይ የተቀመጠው ጽሑፍ በዴች ቋንቋ የተጻፈ በመሆኑ ወፉ ከሆላንድ አገር መምጣቱ ታወቀና የኢትዮጵያ መንግሥት ከሆላንድ መንግሥት ጋር ግንኙነት በማድረግ ያንን ወፍ በአውሮፕላን አሳፍሮ ወደ አገሩ መመለሱ በኢትዮጵያ ዜና መነገሩን እናስውሳለን፡፡ ይህ ወፍ በአገራችን ካሉ በብዙ ሚሊዮን ከሚቆጠሩ ወፎች እንዲያውም በሌሎች በአገሮች የማይገኙ ከተባለትና አገራችንን የቱሪም መገኛ እንትባል ካደረጉ ብርቅዬ ወፎች ሁሉ ተለይቶ የሁሉን ትኩረት የሳበበት ምክንያት ምንድነው ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ ይህ ወፍ በአንገቱ ላይ የተንጠለጠለው ታግ ባይኖረውስ ኖሮ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዩ ግምት ሰጥቶ ወደ ሆላንድ አገር ይመልሰዋል ማለት እንችል ይሆን፣ ምናልባት በዓይነቱ የተለየ ወፍ በአገራችን ተገኘ ተብሎ ከመወራት ያለፈ ነገር ሊደረግለት ባልቻለ ነበር፡፡ በተሸከመው ምልክት ምክንያት ያ ሁሉ እንክብካቤ ተደርጎለት ክብርም አግኝቶ ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡
ይህ ለእኛ ለጌታ አገልጋዮችና ምዕመናን ሁሉ ልዩ ትምህርት ሊሰጥ የሚችል ምሳሌ ነው፡፡ የማንነታችን ማረጋገጫ ፣ ከሌላው የዓለም ሕዝብ የምንለይበት መለያ ምልክት ምንድነው፡፡ የጌታ የሱስ መሆናችን ተለይቶ የሚታወቀው በምንድነው፡፡ የሚያዩ ሁሉ የሚማረኩበት ኢየሱስን በእኛ የሚያዩት ስለ እኛ የሚመሰክሩበት ምልክታችን ምንድነው? ስብከታችን ወይስ ወደ ቤተክርስቲያን አውትረ መሄዳችን? በጉባኤ መገኘታችን ወይስ ብዙ መማራችን? ይህ ሁሉ አስፈላጊና መልካም ነው፡፡ ሰዎች ማን እንደሆኑና ከየት እንደሆኑ በምን ዓይነት ልምምድ ውስጥ እንዳሉ በሰውነታቸው የሚታዩና የሚለጠፉ ነገሮች፣ የተለበሱ ልብሶች ለይተው ያሳዩአቸዋል፡፡ ካህናት በሚብሱት ልብስ፣ ናዝራውያን በጸጉራቸው፣ ዜማውያን በልብሳቸው፣ የመንግስት ታማኝ ታደሮች በትከሻቸው ላይ ባለው የማዕሬግ ምልክቶቻቸው፣ ተለይተው ይታወቃሉ፡፡ ህንጸዎችም እንደዚሁ፣ ለምሳሌ ትምርት ቤቶች፣ መስጊዶች፣ ቤተክርስቲያናት ፣ የጦር ካምፖች፣ ሆስፒታሎች፣ ጤና ኬላዎች፣ ሆቴሎች በላያቸው በተተከለው ምልክት ምክንያት ምንነታቸውና ባለቤትነታቸው ተለይቶ ይታወቃል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ እኛ የኢየሱስ ክርስቶስና ለእርሱ አልግሎት ራሳችንን የሰጠን መሆናችን የሚታወቅበት ምልክታችን ምንድነው?
ሓዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ በሥጋችን ስለ ምንሸከመውና ተለይተን ስለምንታወቅበት መለያችን በገላትያ 617፣ ሐዋ 9 10 -16፣ እና 2ቆሮ 411-16 ባሉ ክፍሎች እንዲህ ይላል፡፡ አነባለሁ የጌታችንን ቃል፡፡ ከጳውሎስ አጠቃላይ ትምህርቶች በአጭሩ የተወሰኑ ነጥችን እንመለከታለን፡፡
1. በሥጋችን የምንሸከመው የኢየሱስ ማህተም ነው፡፡
እኔ የኢሱስን ማህተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ፡፡
ይህ አንድ ዓረፍተ ነገር ነው ፣ ነገር ግን ትልቅ መንፈሳዊ ምሥጥር ያዘለ መልእክት ነው፡፡ አጭር አሳብ ነው ግን የጳውሎስን ሕይወት ከደህንነቱ እሰከ ሕይወቱ ፍጻሜ ድረስ ያለውን ዓላማ ሁሉ ተቅልሎ በውስጡ የያዘ አሳብ ነው፡፡ የጳውሎስ ብቻ ሳይሆን የእኛን የሁላችንንም ሕይወት፣ አገልግሎት፣ ትምህርት ፣ ስብከት ፣ በምድር ላይ የምንኖርበትን የኑሮ ዓላማ ሁሉ የሚያሳየን አሳብ ነው፡፡ ያውም በሰውነታችን የምንሸከመው የማንነታችን መለያ ፡፡
ሐዋሪያው ጳውሎስ በገላትያ አውራጃዎች የጌታን ወንጌል ሰብኮ ቤተ ክርስቲያናትን ከተከለ በኋላ ሌሎች ሌላ ወንጌል የሚሰብኩ ሐሰተኛ አስተማሪዎች ተነስተው ጳውሎስ እውነተኛ ሐዋሪያ ስላይደለ የሚሰብከው ስብከት ትክክል አልነበረም ብለው አስተማሩ:: ደህንነት የሚገኘው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን በጸጋው ብቻ መሆኑን ያስተማረውን የጳውሎስን ስብከት በማጣጣል ደህንንት የሚገኘው ሕግን በመጠበቅ፣ በመገረዝና በመልካም ሥራ ነው በማለት ምዕመናንን ከእውነተኛው ትምህርት ዘውር አድርገዋል፡፡ ይህንን የነፋቄ ትምህርት ሲሞግት ከቆየ በኋላ የገላትያን መጽሐፍ ሲያጠቃልል እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አያድክመኝ በማለት ይናገራል፡፡
ለኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ሓዋሪያ የመሆን፣ እውነተኛ ለመሆኔ ምንም ጥርጥር የሌለው በሥጋዬ የተሽከምኩት ምልክት አለኝ፡፡ ይህ ምልክት ሌሎች የኑፋቄ አስተማሪዎች የሌላቸው ምልክት ነው፡፡ ይህን ምልክት ጳውሎስ ማኀተም ብሎታል፡፡ ጳውሎስ ይህ ምልክት የኖረበት ምክንያት ምንድነው ለሚለው የተለያዩ ምክንያች ይኖራሉ፡፡ አንደኛው በልስጥራና በደርቤ ወንጌልን በሰበከበት ወቅት ተቃዋሚዎቹ ክፉኛ ከደበደቡት በኋላ ከከተማው ውጭ ጎትተው እንደጣሉት የገላትያ ሰዎቸ ራሳቸው ያውቃሉ፡፡ ጳውሎስ እንደዚያ የተደበደበው የወንጌል ስብከት ሥራውን በተቃውሞ ውስጥ በመስበክ ለኢየሱስ ያለውን ታማኝነት በመግለጹ ምክንያት የተደረሰበት ስለሆነ በድብደባው ምክንያት በሰውነቱ ላይ የተፈጠረውን ጠባሳ ማኅተም ብሏል፡፡ እንዲያውም እርሱ አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ ( 2 ቆሮ 12 ) እንዳለው ይህ ድርጊት በተፈጸመበት ወቅት በሰውነቱ ላይ ከግርፋቱ የተነሳ የከሰተው ጠባሳ ለሁሉም ሰው የሚታይ ሲሆን ያ ደግሞ ለጌታ ኢየሱስና ለወንጌል አገልግሎት ባለው መሰጠት ምክንያ የመጣበት ነው፡፡ ይህንን በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ማንም አያድክመኝ ይላል፡፡ እኛ የጌታ ታማኝ መሆናችንን ሰዎች ሁሉ እንዲያቁልን በዚህ ዘመን የግድ የግርፋትን ጠባሳና ገጣባ ለሰው ሁሉ በሚታይ የሰውነት ክፍላችን መኖር አይኖርብንም፡፡ ነገር ግን ማኅተም የሚለው ሌላ ቁልፍ አሳብ አለ፡፡ እርሱም ከማንም ጋር ድርድር የማናደርግበት የድንነታችን ጉዳይ ነው፡፡ በጌታ ያለንን ደህነንትና ሕይወት ማንም ይሁን የማንም ትምህርት እንዲያጎድፍብን አንፈቅድለትም፡፡ ይህ ማሕተም የጌታ የመሆናችን ማረጋገጫ ነው፡፡ ይህንን በኤፌሶን 113-14 እንመለከታለን፡፡ ከምንም በላይ የደህንንታችንና ስደህንነታችን የሚሰጠው ትምህርት ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት በምንም የሚለና ከምንም ጋር የምናወዳድረው አይደለም፡፡ ስለዚ ነው ጳውሎስ የጌታ የኢየሱስን ማኅተም ሥጋዬ ተሸክምአለሁና ማንም አያድክመኝ የሚለው፡፡ ማተም የባቤትነት ማረጋገጫ ነው፡፡ የማን እንደሆንን እና ለየትኛው ዜጋ እንደሆንን የማያን ሰዎች የሚለዩን በያዝው መታወቂያ ወይም በታታመበት ማሕተም ነው፡፡ የበግ ነጋዴዎች በጅላ ካጫኑቸው በጎች ውስጥ የየራሳቸውን በጎች ለይተው የሚያውቁት በበጎቹ ጀርባ ላይ በቀቡት የቀለም ማሕተም ነው፡፡ ለእኛ ደግሞ ለእግዚአብሔርና ለመንግሥቱ የተለየን መሆናችን የሚታወቅበት ትልቁ ማኅተማችን በሥጋችን የተሸከምነው የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው፡፡
2.     የጌታችን የኢየሱስን ስም ነው(ሐዋ 910-16)
በደማስቆ ሐናንያ የሚሉት አንድ ደቀመዝሙር ነበር፣ ጌታም በራዕይ ሓናኒያ ሆይ አለው፡፡ እርሱም ጌታ ሆይ እነሆኝ አለ፡፡ ጌታም ተነስተህ ቅን ወደሚባለው መንገድ ሂድ በይሁዳም ቤት ሳውል የሚባል አንድ የጤርሴስ ሰው ፈልግ፡፡ እነሆ እርሱ ይጸልያልና ሓናንያ የሚሉት ሰው ገብቶ ደግሞ እንዲያይ እጁን ሲጭንበት አይቷል አለው፡፡ ሐናንያ መልሶ ፣ ጌታ ሆይ በኢየሩሳሌም በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ከብዙዎች ሰምቻለሁ ፣ በዚህም ስምህን የሚጠሩትን ለማሰር ከካህናት አለቆች ሥልጣን አለው አለ፡፡ ጌታም ይህ በአሕዛብም ፣ በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፣ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁ አለው፡፡
ጌታ ኢየሱስ ከጳውሎስ ምን ፈልጎ እንደጠራው ይህ አሳብ ይነግረናል፡፡ ጳውሎስ በአህዛብ አገሮች ቤተ ክርስቲያናትን ተክሏል፡፡ ብዙ ሰዎችን የጌታን ቃል አስተምሯል፡፡ እደነ ጢሞቴዎስ ያሉት ደመዛሙርትና የቤተ ክርስቲያን መጋቢያንን አፍርቷል፡፡ እንደምናየው ዛሬም ለቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት የሚሆኑ 13 የሚያህሉ መልእክቶችን ጽፎ አል፡፡ በተዘዋወረባቸው አገሮችና መንደሮች ሉ ተአምራቶችን ሁሉ አድርጓል፡፡ እነዚህ ሁሉ ሥራዎቹ የተጠቃለሉት በአህዛብም በነገሥታም፣ በእሥራኤልም ልጆች ፊት የጌታን ስም በመሸከም ውስጥ ነው፡፡ እነዚህን ሁሉ ልናደርጋቸው የተገባን ቢሆንም ከሁሉም በላይ የጌታን ስም የምንሸከምለት ዕቃው ንድንሆን ይፈለግብናል፡፡ ዛሬ አማኞች በምንኖርበት የክርስትና ሕይወታችን የጌታ የኢየሱስ ስም ከፍ ብሎ ይውለበለባል ወይስ ይሰደባል? መቅረዝ የሚባል ዕቃ አለ፡፡ ይህ መረዝ የሚባው ዕቃ በአድ ቤት ውስጥ መብራትን ከፍ አድርጎ የሚሻከም ነው፡፡ መቅረዙ መብራቱን ከፍ አድርጎ ሲሸከም መብራቱ ሲታ እርሱም አብሮ ይታያል፡፡ መብራቱ ካታየ ግን መረዙ ምንም ክብር ሊኖረው እንደማይች ሁሉ እኛም የኢየሱስን ስም ካተሸከምን ከክርስቶስ የሚጣውን ክብር ልናይ አንችልም፡፡ ወገኖቼ ሆይ ዛሬ ራሳችንን የጌታ ዕቃ አድርገን አቅርበናል ወይ? ክቡር ስሙን ለመሸከም የተመረጥን ዕቃዎች መሆናችንን አውቀን ስሙን እተሸከምን ነው ወይስ ራሳችንን እያወጅን ነው? በየቤተ ክርስቲያናችን መድረክ ኢየሱስ ይሰበካል? መድረክ ስንወርሰድ ሰዎች ኢየሱስን እንዲመለከቱ ስሙን እንዲጠሩ ፣ በስሙ እንዲታመኑ ፣ የኢየሱስ ብቻ ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ ስሙን ከፍ እያወጅን ነው ወይስ የእኛ ስም እያወጅን ነው? ተሸካሚ ዕቃ ለራሱ አይኖርንም ለተሸከመለት ጉዳይ ይኖራል ምክንያቱም ዕቃ ነውና፡፡ የሚታየው እርሱ አይደለም ያ የተሸከመው እንጂ፡፡ ተሸካሚው ምንዜም ከታች እንጂ ከላይ ሊሆን አይችልም፡፡ እኛ ከታች ሆነን የጌታ ስም በእኛ ላይ ሆኖ ሰዎች ሁሉ ይህንን ስም በሰውነታችን፣ በሕይወታችን ፣ በአካሄዳችን አኗኗራችን ያዩታል ወይ?
3. የክርስቶስን ሞትና ትንሳኤ ነው( 2 ቆሮ. 4 7-16)
የኃይሉ ታላቅነት ከእግዚአብሔር እንጂ ከእኛ እንዳይሆን ይህ መዝገብ በሸክላ ዕቃ ውስጥ አለን፡፡፡ በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፣ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፣ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፣ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፡፡የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁል ጊዜ የኢየሱስን ሞት በሥጋችን ተሸክምን እንዞራለን፡
ይህን አሳብ ለመግለጸው ሐዋሪያው ጳውሎስ ከቀጥር 7 ጀምሮ በጣም አስደናቂ ነገር ይናገራል፡፡ በእኛ እግዚአብሔር የሚሠራው ሥራ የሚያስገርም መሆኑን ሲያመለክት  እንዲሁም ደግሞ አንድንም ነገር በራሳችን ብርታት እንዳላደረግነው እንድናውቅ ያሳስበናል፡፡ የኃይሉ ታላቅነት ከእኛ እንዳይደለ እንድናውቅ ያሳስበናል፡፡ በዓለም ላይ ብርቱዎች የተባሉ ብዙዎቸ እያሉ እግዚአብሔር አምላክ የክብር መዝገቡን ሸክላ በሆንንው በእኛ ውስጥ እንዳስቀመጠ ይናገራል፡፡ ሸክላ ምንም ክብር የሌለው ነገር ነው፡፡ በጣም ደካማ ነገር ነው፡፡ አንዴ ወድቆ ከተሰበረ መልሶ መጠገን የማይችል በጣም አሳዛኝ የሆነ ዕቃ ነው፡፡ ሸክላ ከአር የሚሠራ ነው፡፡ ሸክላ ደካማና አቅመ ብስ ነው፡፡ ሸክላ ብዙ ክብርም የሚሰጠው ነገር አይደለም እንዲም የሸክላ ዕቃ የሚሠሩ ሰዎችም ጭምር በሌሎች ዘንድ ክብር የማያገኙባቸው ብዙ ሁኔታዎች አሉ፡፡ ግን የሚገርመው ነር ቢኖር ይህ ደካማ የሆነ ተሰባሪ ዕቃ ውድ የሆነውን ነገር ለመሸከምና በውስጡ ለመጠበቅ መመረጡ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች በሸክላ ዕቃ ውስጥ ወርቃቸውን ይኖሩታል፣ ብራቸውን ያስቀምጡበታል፣ ጌጣቸውንም ይደብቁበታል፡፡ ሽካላ ዕቃ ተሰባሪና የተናቀ ደካማ ነው ግን በጣም ውድ ለሆነ አገልግሎት ይውላል፡፡ በጥንት ጊዜ የእግዚአብሔር ሰዎች በጣም አስፈላጊ የሆነ የብራና ጽሑፋቸውን መሸሸግ ባስፈለጋቸው ወቅት በእንሥራ ( በሸክላ ዕቃ) ውስጥ አድርገው በዋሻ ስለሸሸጉት ሰነዱ ሳይጠፋ ለዘመናት እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ዕቃው ሸክላ ነው ግን ለክቡር አገልግሎት ተፈለገ፡፡ ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ በኩል ባለው በረሀማ አካባቢ የኖሩ ኩምራን ሶሳይቲስ የተባሉ በሚኖሩበት ኩምራን  ዋሻ ውስጥ የተገኘው የሙት ባህር ጥቅል የተባለው ብራና የተገኘው በዋሻ ውስጥ በሸክላ ዕቃ ውስጥ ታሽጎ ነበር፡፡ ይህ የሙት ባህር ጥቅል የተሰኘው ብራና ትክክለኛ የሆኑ ብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በውስጡ የያዘ የጥንት  ጽሑፍ ሲሆን ለበርካታ ዘመናት ተደብቆ የቆየውና ከመቃጠልና ከመውደም የተረፈው በሽክላ ዕቃ ውስጥ ነበር፡፡ በጊዜው የነበሩ ሰዎች ያንን ስክሮል ለመሸሸግ ለምን የሸክላ ዕቃ እንደመረጡት ባይገባኝም ግን ታሪኩ በጣም ያስደንቀኛል፡፡ ወገኖቼ ሆይ እግዚአብሔር አሁንም እያደረገ ያለው ይህን ነው፡፡ የእርሱን ታላቅ ሥራ በሚያምኑትና በማያምኑት ሁሉ ዘንድ ለማስፈጸም እኛን ደካሞችን፣ ሸክላዎችን፣ ተሰባሪዎችን መረጠና ክቡር መዝገቡን በእኛ ውስጥ አኖረው፡፡ ለምን? የእርሱ ሥራ በሰው ኃይል እንደማይከናወን ንዲወቅ ነው፡፡ ኃይል የእግዚአብሔር እንጂ የእኛ እንዳይደለ እንዲታወቅ ነው፡፡ በዓለም ስንኖር ይህ የክብር መዝገብ እያለ በሁሉ እንገፋን፣ እናመነታለን፣ እንሰደዳለን፣ እንወድቃለን ይላል፡፡ ይን እንጂ አንጨነቅም፣ ተስፋ አንቆርጥም፣ አንጠፋም ይለናል፡፡ ምክንያቱም ጌታ በውስጣችን ላስቀመጠው መዝገቡ ስለሚጠነቀቅ ነው፡፡
ጳውሎስ ይህንን አስደናቂ ነገር ከተነናገረ በኋላ አሁንም በሥጋችን ስለምንሸከመው ጉዳይ ይናገራል፡፡ እንዲያው በሥጋችን የኢሱስን ሞትና ሕይወት ተሸክምን ንዞራለን፡፡ የኢየሱስ ሕይወት በሰውነታችን እንዲገለጥ የኢየሱስን ሞት ዘወትር በሰውነታችን ተሸክመን እንዞራለን ይላል፡፡ ወንጌልን በመስበካችን ምክንያት የተለያዩ መከራዎች ቢደርሱብንም እንደሚደርሱብን መከራዎች ብዛት መጠን አንጠፋም ምክንያቱም ለደካማው የሸክላ ዕቃ የእግዚአብሔር ርዳታ ስለማይለየው ነው፡፡ ከዚህም በላይ በመገፋት ፣ በማመንታት፣ እና በስደት ውስጥ በምናልፍበት ጊዜ ሁሉ እኛን በሚያዩን ሁሉ ፊት የኢየሱስ ሞት በሰውነታችን ተሸክመን እንዞራለን፡፡ ይህንን የምናደርገው የኢየሱስ ትንሣኤ በሰዎች ሁ ዘንድ እንዲታወቅ ነው፡፡ በወንጌል አገልግሎታችን ምክንያት ለሞት አልፈን የምንሰጥ ቢመስለንም ግን የኢየሱስን ሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን ይላል፡፡ እንዞራለን ማለት ምን ማለት ነው በሚያዩን ሁሉ ዘንድ ፣ የምንመላሰው የኢሱስን ሞትና ትንሣኤ እያጅን ነው፡፡ የቤተ ክርሰቲያን በምድር የመኖሯ ዓላማ የኢየሱስ ክርስቶስን ሞትና ትንሳኤ ለሁሉም ማወጅ ነው፡፡ እኛ ይህንን እድናደርግ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡
የቤተ ክርስቲያን ትልቁ ጥሪ የጌታችንን የኢየሱስን ሞትና ትንሣኤ በዓለም ላይ ከፍ አድርጋ መሸከም ነው፡፡ የክርስቶስን ሞትና ትንሳኤ መስበክ ከጳውሎስ በፊት ሆነ ከእርሱ በኋላ የነበሩ ነቢያትና ሐዋሪያት ቁልፍ ተግባርና የተልዕኮአቸው ማእከል እንደሆነ  ቅዱሳት መጸሕፍትን በምናነብበት ጊዜ የምናገኘው ነው፡፡ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው ነቢይ የነበረው መጥመቁ ዮሐንስ ከኢየሱሰስ በፊት የመጣ ነበር፡፡ እርሱ መንግሥተ ሰማይ ቀርባለችና ንሰሐ ግቡ እያለ ለንስሐ በውሃ እያጠመቀ በዮርዳኖስ ወንዝ ዙሪያ በሰበከበት ወቅት አንድ ምቹ አጋጣሚ አግኝቶ ነበር፡፡ ያውም ሰዎች አንተ ማነህ ፣ መሲሁ ነህን? ኤልያስ ነህን፣ ኤርምያስ ነህን፣ ነቢዩ ነህ እያሉ ሲጠይቁት ሁሉንም አይደለሁም ነው ያላቸው፡፡ ስለራሳችን ዝና፣ ክብርና ሞገስ እንደምንኖረው የዛሬው ዘመን አገልጋዮች ቢሆን ኖሮ ስለ ራሱ ብዙ መናገርና ብዙ ክብር ማግኘት ይችል ነበር፡፡ ግን አይለደለሁም አለ፡፡ ታዲያ ማን ነህ ሲሉት እኔ ለንስሐ በውሃ አጠምቃችኋለሁ፣ ከእኔ በኋላ የሚመጣው አጎንብሼ የእግሩን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ከእኔም የሚበረታ መንፈስ ቅዱስና በእሳት የሚያጠምቃችሁ ነው አለ፡፡ ኢየሱስ ሲመጣ ኣይቶ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያወግድ የእግዚአብሔር በግ ብሎ ወደ ኢየሱስ አመለከተ፣ እንዲያውን እርሱ ሊልቅ እኔ ላንስ ይገባኛል ብሎ ክብርን ለኢየሱስ ሰጠ እንጂ ከራሱ ባገኘው አጋጣሚ ክብርን ሙገሳን አልወሰደም፡፡ ስለዚህ ከሴቶች ከሚወለዱት መጥመቁ ዮሀንስን የሚበልጥ የለም ተባለለት፡፡ ጌታ ሲከብር እርሱም አብሮ ከበረ፡፡
ሐዋሪያው ጳውሎስም አንደዚሁ ነው፡፡
የኢየሱስን መኅጸም በሥጋዬ ተሸክሜአሁ፣
ግሪኮች ጥበብን ይሻሉ፣አይሁዶች ምልክትን ይፈልጋለሉ እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እሰብካለን፡፡
ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ሞትም ጥቅም ነው
ለእኔ ረብ የነበረውን ሁሉ ስለ ክርስቶስ እንደ ጉዳት ቆጥሬዋለሁ …. እርሱንና የትንሳኤውን ኃይል አውቅ ዘንድ ቢሆንልኝ በሞቱ እንኳ እመስለው ዘንድ እነፍቃለሁ
ከጌታችን ከኢየሱስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ራቅ አለ፡:
እኔ ክርስቶስን እንደሚመስል እናንተ ደግሞ እኔን ምሰሉ
በቆላስይስ መልእክት ብቻ ከ18ጊዜ በላይ ክርስቶስን የበላይነት ጠቅሷል፡፡
አንዳንድ ይወታቸው ለጌታ ያልታመኑ ሰችን ሲገልጽ ሁሉ የራሳቸውን ይፈልጋሉ የክርስቶስ ኢየሱስን ግን አይደለም፡፡ ፊል 221
18ኛው ክፍለ ዘመን የፑሪታን አባት ተብለው ሚጠሩ ዊሊያም ፔርክስ የተባሉ የሥነ መለኮት ሰው ትምህራቸውና የሕይወታቸው መፈክር ለክርስቶስ፣ በክርስቶሰ፣ ስለ ክርሰቶስ የሚል ነበር፡፡ በቅርቡ ከሁለት ዓመት በፊት ገዳማ ወደ ጌ የተጠሩት የእግዚአብሔር ሰው ጆን ሰቶትም ክርስቶስ ካተሰበከ ስብከቱ አልተሰበከም፡፡ ክርቶስ ካልዘመረ ዘማሪው መዝሙሩን አልዘመረውም፣ ክርስቶስና ስሙ ካታከሉበት ሎቱም አልተጸለየም ብለዋል፡፡
4. የጌታ የኢየሱስን መስቀል መሸከም፡፡ ማቴ. 1624-28፣ ሉቃስ 9 23-24
ሰዎች ጌታን እንደተቀበሉ መጀመሪያ የሚሰጣቸው ትምህርት የደቀመዝሙርነት ትምህርት ነው፡፡ ጌታ ማንም እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር መስቀሌን ይሸከም ያለውን ትምህርት አማኞች የው ጥምቅ እስክ ወስዱ ድረስ ብቻ ብቻ እናስተምራቸዋለን፡፡ ከዚያ በኋላ ላለው የክርስትን ሕይወት ዕድገት ደረጃዎች ውስጥ እንደማያስፈልገን አድርገን እንመለከተዋለን፡፡
ይሀን እንጂ የጌታን መስቀል መሸከም እስከ ሕይወታችን ፍጻሜ ድረስ የምንተገብረውና የማናቋርጠው ጉዳይ ነው፡፡ ክርስትና ደስ የሚል የሕይወት ጉዞ ቢሆን መስቀል የመሸከም ግዴታ ያለበት መሆኑ ደግሞ ሌላው ገጽታው ነው፡፡ በክርስትና ሕይወት ጦርነት ድል፣ ያለ መስዋዕትነት ክብር ፣ ያለመሰጠት በረከት የለበትም፡፡ ስለዚህ ክርስትና እንዴት ያለ ቅድመ ሁኔታ የሚፈልግ እንደሆነ እንመለከታለን፡፡ ኢየሱስ  በዚህ ሥፍራ ምንም እኔን ለመከተል የሚወድ የሚወድ ቢኖር  የሚል ቃል ተጠቅሞአል፡፡ በሌላ ሥፍራ ደግሞ ከኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር አለ፡፡ ይህ ማለት ምን ማለት ነው; ማንም ክርስቲያን ሊሆን የሚፈልግ ማለቱ ነው፡፡ ምክንያቱም ክርስትና የጥንት ስሙ መከተል ወይም መንገድ ነበር፡፡ ደቀ መዛሙርቱ በአንጾኪያ ክርስትና ከመባለቸወው በፊት ክርስትና መንገድ በመባል ይታወቅ ነበር፡፡ አማኞችም ደግሞ የመንገዱ ሰዎች ተብለው ይጠሩ ነበር፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ እኔን መከተል የሚወድ ወይን ከኋላዬ ሊመጣ የሚወድሲል ክርስትያን መሆን የሚወድ ወይም የሚፈልግ ማለቱ ነው፡፡ ክርስትና መሆን ደግሞ የአንድ ጊዜ ሞቅታ የሚያመጣው ሳይሆን ሁል ጊዜ የምንተገብረው ነው፡፡ የኢየሱስ ተከታይ መሆን ፣ የእርሱ ተማሪ መሆን  የክትትል ትምህርት ጨርሰን ወደ አገልግሎት መሥመር እስክንገባ ድረስ ብቻ የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ኢየሱስን የምንከተው ፣ በመንገዱም የምንራመደው በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ነው፡፡
እህግዲህ ይህ አሰብና እውነት ዛሬ ተረስቷል፡፡ አንዳንድ ጊዜ  ወደ አገልግሎት ደረጃ ከደረስን ምንም ከክርስትና አኗኗር እንደተመረቅን ይሰማናል፡፡ ግን የእግዚአብሔር ቃል መስቀሉን መሸከም ያለብን በየዕለቱ እንደሆነ ይነገረናል፡፡ በየዕለቱ እንምንዘምረውና እንደምናገልግለው ሁሉ በየዕለቱ የጌታን መስቀል እንሽከማለን ማለት ነው፡፡ መስቀሉን ሳይሸከሙ በኢየሱሰስም ንገድ ሳይሄዱበት የሚያገልገልሉት አገልግሎት ለእግዚአብሔር ክብር አይሆንም ለምዕመናንም አይጠቅምም፡፡ በኢየሱስ መንገድ ሳይሄዱበት የሚደረገው አገልግት፣ ዘማሪነት፣ ሰባኪነት፣ አስተማሪነት፣ መሪነት ሁሉ  ለቤተከርስቲን እጅግ በጣም ጠንቅ ነው፡፡ የዛሬዋ ቤተክርስቲያን ትለቁ ችግር የአገልጋዮችና የመሪዎች ችግር ሳሆን በሕይወታቸው ጌታን የማይከተሉ አገልጋዮችና መሪዎች የተበራከቱ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ለመሆኑ በሕይወታቸው ኢየሱስን የማይተሉ መሪዎችና አገልጋዮች ሊኖሩ እንደሚችሉ እናውቃለንን;
የኢየሱስ መሆናችንና በመንገዱ የመሄዳችን ትልቁ መሥፈርት አንዱ ራስን መካድ ነው፡፡ ራሳችን ካልካድን የእርሱን መንገድ መምረጥ እንችልም፡፡ ሰው ወደ ጌታ ሲመጣ ራሱን ሲክድ ብቻ ነው ኢየሱስ በልቡ የሚነግሰው፡፡ ሰዎች ክርስትያኖች አንዲሆኑ እናስተምራቸውና ራሳቸውን እንዲክዱ ስላላገዝናቸው ማነታቸውና እነርሱነታቸው በውስጣቸው ይኖራል ፣ ሲያድጉም ያ እኔነታቸው አብሮ እያደገ እየጎመሰ ይሄድና የክርስቶስን ቦታ ይይዝባቸዋል፡ ከዚህ የተነሳ በሕይወታቸው ጌታን ሌለሎች ማሳየት ያቅታዋል፡፡ ምክንያቱም በልባቸው ዙፋን ላይ ፣ በሕይወታቸው የውስጠኛው ክፍ ላይ ቦታውን የያዘውና የሞላው ጌታ ኢየሱስ ሳይሆን እኔነቻው ነው፡፡ እኔን አወድሱኝ የሚሉ መጋቢዎች ገጥሞአችሁ አያውቁም; እኔ ነኝና ባለመፍትሔው እኔን ብቻ የሚሉ አገልጋዮች ገጥሞአችሁ አያውቁምእነዚህ ራስን ያለመካድ  ችግር ተጠቂዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ራሳችንን በካድን ጊዜ እኛ ሳንሆን እገዚአብሔር ብቻ ሕይወታችንን ሊያድን እንደሚችል አውቀን ራሳችንን በእርሱ እጅ ላይ ወደምንጥልበት የአቅም ደረጃ እናድጋለን ማለት ነው፡፡ ስላራችንን ያለንን የተሳሳተ ግምት ትተን ፣ ሰይጣንም የሚሰጠንን ፍቅር ሁሉ ወደ ጎን በመተው በክርስቶስ ፍቅር ወደምንታሰርበት ካፓሲቲ እያደግን እንሄዳን ማለት ነው፡፡ በአንጸሩመ ደግሞ ራሳችንን ወደ ማገሱና መሸሙ ደረጃ በደረሽን ቁጥር ጌታን ከልባችን ዙፋንና የክብር ሥፍራ ወደ ማውረዱ ደረጃ እየተሸጋርን እሄዳለን ማለት ነው፡፡ ሰዎች የእግዚአብሔር ነገር እንደተወሰደባቸው ከሚታወቅበት መንገድ አንዱ እኔ እኔ እኔ ሲሉ ነው፡፡ በእኔነት የተሞላው ሰው ጌታ ኢየሱስን ለሌሎች ማሳየት አይችልም ምክንያቱም ሰው በውስጡ ከሞላው ነገር ያፈሳልና፡፡
ሁለተኛው መሥፈርት ፈቃደኝነት ነው፡፡ የሚወድ ቢኖር ( የሚፈልግ ቢኖር) የሚለው አሳብ በጣም አስፈላጊ ቃል ነው፡፡ ሁሉም ነገር በራስ ውሳኔ በፈቀደኝነትና በፍቅር ነው፡፡ ይህ ማኛውንም ነገርለማድረግ የሚያስችለን ነገር ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሆነ ሰይጣንም የራሳቸውን መንገድ እንድንከተለ የሚያደርጉን በፍቅር ነው፡፡ ለምሳሌ ጌታ ኢየሱስ የእርሱ ተለታች የሚየደርገን በፍቅር ነው፡፡ ሰጣን ደግሞ የራሱ ተከታዮች የሚያደርገን ፍቅርን በማሳየት ነው፡፡ ሰይጣን ፍቅርን የገለጠበት መንገድ ኢየሱሰስ ፍቅርን ከገለጠበት መንገድ ይለያል፡፡ ይህንን ነው አማኞች መለየትና መንቃት ያቃተን፡፡ ኢየሱስ ምክንያታዊ ባልሆነ ፍጹም ፍቅር ወደደን፡፡ እኛን አብልጦ ከመውደዱ የተነሳ ክቡር ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ክቡር ደሙንም ስለ እኛ አፈሰሰልን፡፡ ሰይጣን ደግሞ ፍቅር የገለጠው  ሰዎች ብቻ አፍቃሪዎች እንዲሆኑ በማድረግ ነው፡፡ የገንዘብ አፍቃሪዎች፣ የክብር አፍቃሪዎች፣ የዝሙት አፍቃሪዎች፣ የዚህ ዓለም አፍቃሪዎች ፣ የዘር የወገን አፍቃሪዎች፣ የመጠጥ የሲጋራ የጫት ፣ ተድላ ወዘተ አፍቃሪዎች እንዲሆን ያደርግና ጌታ የሚያፈቅሩበትን አቅም ይወስድባቸዋል፡፡ እዚያ ውስጥ ግን ሳይታወቅ እየተወደደ ያለው እርሱ እንደሆነ ማንም ላያስተውል ይችላል፡፡ ለሰዎች ደግሞ የሚያምራቸው መንገድ ሰይጣን የገለጠው መንገድ ነው፡፡ ስዚህ መከራን ፣ ችግርን፣ ስዴትን ልፋትንና መንፈሳዊ ጦርነትን እንዲሁም መስዋዕትነትን የሚጠይቀውን የኢሱስን መንገድ ለጊዜውም ዞር አድርገው ይሕንን በጣም ማራኪና ናፋቂ የሆነ ልፈትና እንግልት የሌለበትን የፍቅረር መንገድ መከተል ይላቸዋል፡፡
ሌላው እንግዲህ መስቀሉን መሸከም ነው፡፡ ምንድነው መስቀሉ;  መስቀል የመሸከም ጉዳይ ብዙ ጊዜ የማይገባን ምስጥር ይሆንብናል፡፡ ሌላው ቀርቶ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርትም ቢሆኑ ግር ሳይላቸው አልቀረም ምክንያቱም ኢየሱስ መስቀሉን ማይሰከም ለእኔ ሊሆን አይችልም ሲል ገና በመስቀል አልተሰቀለም ነበርና፡፡ ይሁን እንጂ በጊዜው ከኢየሱስ በፊት በመስቀል ላይ የተሰቀሉ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ጌታ ኢየሱስ ለመምጣቱ ምናልባት 120 ዓመታት በፊት ኢንተርተስታሜንት ፒሬድ ተብሎ በሚታወቅው ጊዜ አንቲክዮስ ኤፒፓኔስ በግሪክ መንግሥት ሥልጣን ጊዜ በርካታ አይሁዶችን  በእንጨት ላይ ሰቅሎ ገድሎአቸዋል፡፡ ደግሞ  የሮማውያን ንጉሥ ታላቁ  ሄሮዲስ 2000 አይሁዶችን ሰቅሎአቸዋል፡፡ በኢየሱስ የምድር አገልግሎት  ጊዜ  ሥቅላት በግሪክ፣ በሮማውያን፣ በመካካላኛው ምሥራቅ በግብጾችም ዘንድ በጣ የተለመደ ነው፡፡ እንዲያውም አንዳንዶች 30.000 አይሁድ በስቅላት ተገድለል የሚል ግምት አላቸው፡፡ ይህንን ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ያውቃሉ፡፡ ቢሆንም ኢየሱስ የሚለው ከባድ ሊሆንባቸዋል፡፡ እንዲህ ኢየሱስን መከተል እና የክርስትና ሕይወት መኖር ምን ዓይነት ከባድ እንደ ነበረ የሚያሳይ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ብዙ ሰዎች የመስቀልን ከቁሳዊ ገጽታ በላይ ባለፈ ማየት የሚሳነን ጊዜ ጥቂት አይደለም፡፡ ግን መስቀልን መሸከም ስንል ምን ማለታችን ነው› የክርስትናችን ምልክት ነው አይደለም;፡፡ በደረት ኪሳችን ላይ የምናስቀምጠው፣ በቤተክርስትያናችን ሕንጻ ላይ የምንተክለው፣ በአንገት ብላችን ላይ የምናሳትመው፣ ሌላ ሌላም፡፡ አዎን ውነት ነው ግን በልባችን የሚሳውም እርሱ ሊሆን ይገባዋል፡፡ መስቀሉ ለእኛ ምን ያሳየናል;  ጌታ ኢየሱስ በሄደባቸው መንገዶች ሁሉ ለመሄድ ራችንን የሰጠንበት ሕይወት ተሞክሮ አይደለምን ; ክርስትና እኮ ኢየሱስ የኖረበትን ሕይወት ለመኖር በመወሰን ራሳችንን የምንሰጥበት መርህ ነው፡፡ ይህ መርህ ማቴ 1024 ላይ እንደተቀመጠው ባሪያው እንደ ጌታው ደቀመዝሙሩ እንደ መምህሩ የሚሆኑበት የሕይወት መርህ ነው፡፡ እኛ ኢየሱስስን ለመከተል ስንል ሕይወታችንንና እኛነታችንን ለእርሱ የምንሰጥበት የሕይወት መርህ ነው፡፡
ከዚህም በላይ ጌታ ኢየሱስ ስለ እኛ መከራን የተቀበለበትን፣ የተዋረደበትን፣ የተንገላታበትን የሚያሳይን ነው፡፡ እርሱ በመስቀል ላይ ተወረዶ እኔን ያስከበረበትን፣ የእኔን ነፍስ ሊያረካት ተጠማሁ ያለበትን፣ የእኔን እጅና እግር ለክብሩ ለመማረክ እጅና እግሩን የተቸነከረበትን፣ እኔን ከአብ ጋር ሊያስታርቀኝ እርሱ በአባቱ የተራሳበትንና አባቴ አባቴ ሰልምን ተውከኝ ያለበትን ፣ የእኔን ቁስል ለመፈወስ እርሱ ጀርባው በሮማውያን መጥፎ ጅራፍ አለንገጋ የተተለተከበትን ፣ እኔን የእግዚአብሔር፣ የሰውና የራሴ ጠላት የሆንኩትን ሰው የእርቅና የሰላም ሰው ለማድረግ የሚያደርጉትን አየውቅምና ይቅር በላቸው ብሎ የተማጠነበትንና ያማለደበትን ያንን የክርስቶስን መስቀል በሥጋዬና በነፍሴ ተሸክሜአለሁ፡፡ እንግዲህ ይህንን በሕይወታችን በምንተግብርበት ጊዜ የማነታትችን መለያለሁሉም ያወቃል ማለት ነው፡፡
5. የጌታ የኢየሱስ ቀንበር መሸከም( ማቴ 1129-31)
እኛ የኢየሱስ መሆናችን ከሚታወቅበት መንፈሳዊ ገጽታዎቻችን አንዱ ቀንበር መሸከም ነው፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ብዙ ሰው በክርስትና ሕይወቱ መስቀል ስለመሸከም ይሰማል ቀንበር መሸከም የሚባል ነገር እንዳለ አያውቅም፡፡ ብዙዎቻችን የመስቀል ምልክት አለን ግን የቀንበር ምልክት የለንምምክንያቱም ቀንበርን ስለመሸከም ብዙም ትኩረት ስላለሰጠን ነው፡፡ መስቀልምን መሸከም ያልቻለ ነው ቀንበርንም መሸከም ሊከብድበት ይችላልና፡፡ ምክንያቱም መስቀል ወደ ክርስትና ሕየወታችን ከገባንበት ቀን ጀምሮ የምለማደው ስለሆነ ቀንበር ወደምንሸከምበት ሁኔታ ስንደርስ ቀላል ይሆናል፡፡ መስቀልን መሸከም ያልተለማመደ ሰው ቀንቡም የዚያሀውኑ ያህል ሊከብደው ይችላል፡፡ ግን መሸከም ማን ማለት ነው፡፡ አይሁዶች ቀንበር የሚለውን ቃል የሚወስዱት በአንድ ነገር ውስጥ ለመግባት ራስን ከመስጠት ጋር በማያያዝ ነው( ሳሚሺን) ፡፡ በሐዋሪት ዘመን መሪዎቻቸው ሕዝቡ ሊሸከሙ የማይወዱትን ቀንበር ( ግዴታ) በትከሻው ላይ ይጭኑባቸው እንደነበር ይታወቃል፡፡ ምክንያቱም የሮማውያን አገዛዝና ሥልጣን በሕዝቡ የተወደደ ሳይሆን በግድ ተብሎ የተጫነ ቀንበርና እሥራት ነበር፡፡ ስለዚህ ነው ጌታ ለሕዝቡ ቀንበሩን እሰብራሁ እያለ ተስፋ ይሰጣቸው የነበረው፡፡ መጥፎ ቀንበር፣ የባርነት ቀንበር፣ የጭቆና ቀንበር  ተጭኖባቸው ስለነበር ሕዘቡ ወደ እግዚአብሄር በጮኹ ጊዜ እገዚአብሔር ቀንበሩን  ከትከሻቸው እንሚሰብር ተናረ፣ ያም ቀንበር ደግሞ በጌታ በኢየሱስ ስም ተሰብሮልናል፡፡
ኢሱስ በማጣ ጊዜ ወደ እርሱ የሚመጡትን ቀንበር እንዲሸከሙ ጥሪ አድርጎላቸዋል፡፡ ይህንን ያደረገው ግን በሕይወታቸው ያለውን ከባዱን ቀንበር ሁሉ ከሰበረ በኋላ ነው፡፡ በነፍሳቸውም ያለውን ቀንበርና ሸክም ሁሉ ካወረደላቸው በኋላ ነው፡፡ እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ ፣ እኔም አሳርፋችኋለሁ ብሎ ነው፡፡ የእናንተን መጥፎ ሸክም እኔ አነሳለሁ እናንተ ግን የኔን ቀላልና እረፍት የሚሰጠውን ሸክም የሆነውን ቀንበር በላያችሁ ተሸከሙ ይለናል፡፡  ልክ እንደመስቀሉም ሁሉ ቀንርም ከእንጨት የሚሠራ መሣሪያ ነው፡፡
ቀንበር ለኃላፊነት የምንሰጥበት መንገድ ነው፡፡ ቀንበር የሚሠራውም በሰለጠኑ አናጢዎች እንስሳውን በማይጎዳ መልክ ተለክቶ የሚሠራ ነው፡፡ ከዚያ ቀንበር ሥር የሚሆነው በሬ ሞፈሩን ለመጎተት፣ በገበሬውም ትልም ለመመራት፣ ትልሙንም የመቅደድ ኃላፊነቱን ለመቀበል አቅመ ቢስ ከሆነው ገበሬ እጅ ሥር ራሱን አስገዝቶ በቀንበሩ ላይ ባለው ማነቆ ይተሰራል፡፡  እንደዚሁም ሁሉ የጌታን ሥራ ለመስራት የአገልግሎትንም ኃላፊነት ለመቀበል በፈቃዳችን ራሳችንና ሁለንተናችንን ለጌታ ለኢየሱስ መስጠታችንን የሚያመላት ነው፡፡ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ የሚለው ቃል፡፡
በኢሱስ ጊዜ ለቀንበር የሚሰጠው ሌላው ምሥል ደግሞ መማር ነው፡፡ ተማሪው ሁሉ ጊዜ በራሱ ውዴታ ከመምህሩ ለመማር ይመጣል እንጂ ተማሪ አስገድዶ የሚያስተምር አስተማሪ በፍጹም የለም፣ አይኖርምም፡፡ ስለዚህ አይዶች ቀንበርን ምን ይሉታል የህግ ቀንበር፣ ቶራህ ቀንበር፣የትዕዛዝ ( ኮማድሜንት)ቀንበር፣ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የእግዚአብሔር ቀንበር ብለው ይጠሩታል፡፡  ጌታ ኢየሱሰስም ያኑትን የሚጠይቃቸው አንዱ ጥያቄ ይህ ነው፡፡ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ( ከእኔ ተማሩ ) ይላቸዋል፡፡ የእርሱን ቀንበር መሸከምና ከእርሱ መማር ለት ምን ማለት ነው፡፡ ለእርሱ አመራር፣ ትምህርት ሥልጣን ራሳችንን መስጠት ማለት ነው፡፡  ይህ መታዘዝን የሚያሳይ ቀንበር ነው፡፡ ይህ ቀንበር በክርስትና ሕይወታችን ስንኖር ይንጨነቅበትና የምንጠበብበት ሳይን እፎይ የምንልበት ነው፡፡ ለጌታ ታዘዝና ራሳችንን ለእርሱ መስጠት እረፍትን የሚሰጥ ነው፡፡ ሸክማችሁን ወደ እኔ አምጡ እኔ አሳርፋችኀዋለሁ ብሎ እዳሳረፈ ሁሉ ቀንበሩንም ስንከም ነፍሳችንን ያሳርፋታ ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው ለነፍሳችሁ እረፍትን ታችሁ የሚለን::
ኢየሱስን ቀንበር የመሸከም ሌላው ምስጥር ደግሞ ትብብር ነው፡፡ ከእንዱ ከሌላው ጋር በሕብረት መዋሄድን የሚያመለክት ነው፡፡ ቀንበር በአንድ በሬ ትከሻ ብቻ አይጫንም፡፡ ሁለት በሬዎች ናቸው የሚገትቱት፡፡ የበሬዎቹ ትክለ ቁና፣ እድመሜ ፣ ጉልበት፣ ልምድ፣ ባሕሪያ ወዘተ የተለያየ ሊሆን ይችላ፡፡ እነዚህ የተለያዩ በሬዎችን በአንድ ሥራ ላይ የሚያሰማረው ቀንበሩ ነው፡፡ሁለቱ በቀንበር ሥራ ሆነው አንዳቸው ለሌላው ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ሲሰጡ በእነርሱ ላይ ጌታ የሆነው የገነሬው ሥራ ወይም እርሻው በተሳካ ሁኔታ ይታረሳል ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ከሁለቱ በሬዎች አንዱ እምቢ ያለ እንደሆነ እርሻው ሳይታረስ ሊከርም ይችላል ከቀንበር ምስጥር ይንማረው አንዱ ይህን ነው፡፡ ጌታ ቀንበሬን በላይችሁ ተሸከሙ ሲለን በእግዚአሔር እርሻ ላይ ለመሰማራት አንዳችን ለሌላችን ራሳችን ዝቅ ማድረግን የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በጣም ከባድ ሆኖብናል፡፡ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር አሁንም ይህንን እንድናደርግ ዘንድ ይፈልጋል፡፡ ወንድሞችና እህቶች ሆይ ይህ ታላቅ ምስጥር ነው፡፡ ትልቅ በረከት ያለበት ነው፡፡ ለወንጌላውያን አብያተክርስትያና አገልጋዮች ዘንድ ትልቅ ፈተና የሆነብን ይህ ነው፡፡ ሸክማችንን በኢየሱስ አጠገብ ላመስቀመጥና ለማረፍ በጣ እንመኛለን ግን የእርሱን ቀንበር በሸከም የሚገኘው የነፍስ እረፍት ለማወቅ አልቻልንም፡፡ ሐዋሪው ጳውሎስ ማን ባልንጀራው ከእርሱ እንዲሻል ይቁጠር የሚለው ለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስም እርስ በርሳችሁ ብትዋደዱ ደቀመዛሙርቴ እንደሆናችሁ ሰዎች በዚህ ያውቃሉ ብሏል፡፡ ሰዎች እኛ የኢሱስ መሆናችንን የሚያቁብ መንገድ ወይም መለያ ምልክታችን የእርስ በርስ ፍቅር ነው
6. የቅዱሳንን ሸክም መሸከም ( ገላትያ 625)
የቅዱሳንን  ሸክም መሸከም ማለት ምን ማለት ነው፡፡ ይህ እንዲገባን ዕብራውያን 131-3 ፣ እና ሮሜ 129-16 ያለውን  ማበቡ የተሸለ ነው፡፡ የታሠሩ ሰዎች ሲኖሩ እናንተም ከእነርሱ ጋር በእሥር ቤት እንዳላችሁ አድርጋችሁ ራሳችሁን ተመልከቱ፡፡ ከጌታ ከኢየሱስ ትምህርትና ከመጀመሪያዋ የኢየሩሳሌም ቤከርስቲያን ተግባራዊ አኗኗር የምንማረው አስደናቂ ነገር ቢኖር አንዱ የከመንፈስ ቅዱስ ሌላውን ሸክም መሸከም ነው፡፡ የሐዋሪያትን ስራ 4ን በምመለከትበት ወቅት በበዓለ ሃምሳ ቀን የተከሰተውን የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ተከትሎ በሕይወታቸወ ከታየው አስደናቂ ነገር አንዱ የእርስ በርስ ሸክም መሸካካም ነበር፡፡ አንድም ደሀ በመካላቸው አንዳይኖር ያላቸውን ሁሉ እያመጡ በሐዋሪያት እግር ሥር ያስቀምጡ ነበር፡፡ ለሁሉም እንሚያስፈልጋቸው ያካፍሉ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ የአይሁድ እምነት ወይም የሀይኖት መሪዎች የነበሩ ፈሪሳውያ ደሀዎችን ቤት ፣ የመበለቶችን ቤቶስ ሲበዘብዙ ኣና ሲበሉአቸው ደቀመዛሙርቱና የኢየሩሳኬም ቤተክርስቲያን አማኞች ደግሞ ያቻውን ንብረትን ጥሪት በመሸጥና ወደ ሐዋሪያት በማምጣት ደሀዎችንኛ የተቸገሩትን ይደግፉአቸው ነበር፡፡ ይንን በማደረጋቸው በፈሪሳውያንኛ በመንደፍስ ቅዱስ አማካይነት በሚደረገው እወውነተኛ ርስትና መካካል የሚኖረውን ልዩነት በግልጽ ለማሳየት ችለዋል፡፡ በመከራና በችግር ውስጥ ላለችው ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ገንዘብ አዋጥተው ይሰጡ ነበር፡፡ ይህን የሚያደርጉት ደግሞ ስለ ተረፋቸው ሳይሆን ከድህነታቸው ጥልቀት ሁሉ የኢየሱሰስን ቸር ላጋስነት በተግባራቸው ይገልጡት ነበር፡፡ ይህ ዓይነት ሕይወተወ ለሁላችንም የሚያስፈልግ ነው፡፡፡
ከዕብራውያ ትምህርት እንደምንመለከተው  በክርስቶስ የሆነው ወንድማችን ቢታሠር ያ እሥራት የእኛም ነው ማለት ይኖርባቸዋል፡ የታመመውን ሲያይ ያንን ሕመም አብራችሁ ልትታመሙ ይገባቸዋል፡፡ ይህ የክርስቶስ የመሆናችን መለያ ነው፡፡ የጥንታቤተ ክርስቲያን የምትታወቀው በዚህ ነው፡፡
በወንገጌው ያን አብያተ ክርስቲናት ዘንድ ይህ እነደቀድሞዎቹ ሕዝቦች መሆን እጅግ የተሳነን ጊዜ ቢሆን አሁን ነው፡፡ ዛሬ አንገታቸው እየተቀላባቸው ወገኖች ጉዳይ ፣ የቤተሰባቸው ልቅሶና ሰቆቃ እኛን ለየገነበግብ ይገባናል፡፡ በአፍሪካ ውስጥ በየሰምንቱና በየቀኑ የሚቃጠሉ ቤተ ክርስቲያናት የእኛ ናቸው ፣ እኔ የማመልክባት ቤተ ክርስቲያን ነው የተቃጠለው ማለት ወደምንችልበት የአቅም ደረጃ ከፍ ማለት ይኖርብናል፡፡ ስግብግብነት በጣም አደገኛ እሥራት ነው፡፡ በመካከላችሁ የተቸገሩትን ገልጋዮቻችሁን፣ እህቶቸችሁን ፣ የቤተከርስቲያን አባቶች ፣ የተራቡ በእሥራት ያሉትን በዓለም ዙሪያ በአሁኑ ጊዜ በጣም ብዙ ሰዎች አንገታቸው በክርስትና ምክንያት እየተቀላ ነው፡፡ እነዚያን ከብባችን ልናስብ ይገባናል፡፡ ብዙ ቤተ ክርስቲያን እየተቃጠለ ነው፡፡ የእኔ ቤተ ክርስትያን እደተቃተለ በማሰብ በእግብሔር ፊት አብረን ልናለቅስ ይገባናለ ይህ ሁሉ የክርስቶስ የመሆናችን ምልክት ስለሆን በዚህ ልንተጋ ይገባናል፡፡
የክርስቶስ የመሆናችን ምልክት. የማነታችንና  የምነታችን መለያ ፡፡