Saturday, January 25, 2014

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ (ክፍል ሁለት)

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ ( part two)

በመጋቢ ሳሙኤል ሾንጋ

በተለያየ ዘመናት የነበሩ መንግስታት ከወንጀል ጋር በተያያዘ በወህኒ ለታሰሩ እስረኞች ይቅርታ አድርገው ይለቅቋቸዋል፡፡ ይህ አይነቱ አሰራር በሮማውያን ዘንድ የተለመደና በየዓመቱ የሚከናወን ስለነበረ ኢየሱስ በምድር በነበረበት በአገልግሎቱ መጨረሻ አካባቢ በሰዎች እጅ አሳልፎ ተሰጥቶባለበት ወቅት ከእርሱ ወይም በረባን ከተባለ ሌባ ከሁለት አንዳቸውን ለመፍታት ሙግት የተነሳው ከዚህ ጋር በተያያዘ ነበር ፡፡ በእርግጥ እንዲህ አይነቱ ይቅርታ የሚሰጠው የሕዝብ በዓላት በሚከበሩበት ወቅት ነው፡፡
በአገራችንም የሕዝብ ታላላቅ በዓላት በሚከበርባቸው ወቅቶች በሺህ የሚቆጠሩ እስረኞች ከወህኒ ቤት ተለቀው የወጡበት ሁኔዎች እንደነበሩ ትዝ ይለናል፡፡ መንግስት ቀለል ያለ ወንጀል የሰሩና በትምህርትና በምክር ሊታረሙ የሚችሉ ናቸሙ ብሎ የሚያምንባቸውን ወንጀለኞች ይቅርታ አድርጎ ሲፈታቸው ተመልሰው ከሕብረተሰቡ ጋር ሰላማዊ ኑሮ እንደሚኖሩ በማዘጋጀትና ይህንኑ ተስፋ በማድረግ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ተመልሰው እንደገና እኩይ ተግባራትን ቢፈጽሙ በቀጣዩ የሚጠብቃቸው ቅጣት ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በፊት የነበረው ሪከርድ ተጠቅሶ የፍርድ ሂደቱን ሊያከብድባቸው ይችላል፡፡
በጌታ ኢየሱስ የምድር ዘመን በጣም የሚታወቁ የአይሁድ ሕዝብ አካል የሆኑት የኩምራን ሕብረተሰብ ናቸው፡፡ ኩምራን ግዙፍ ሃይማኖታዊ ሕብረተሰብ ሲሆኑ የራሳው የሆነ የማህበረሰብ ሕግና ደንብ ነበራቸው፡፡ ወጋቸው መሠረት የሚያደርገው የሙሴን ሕግ ፍፁም በማክበር ላይ ሲሆን አንድ ሰው ሆነ ብሎ ወንጀል ቢሰራ ከማህበረሰቡ እስከመጨረሻው እንደሚገለል መመሪያቸው ይደነግጋል፡፡ በተመሳሳይ ሰነድ ውስጥ ደግሞ እግዝአብሔር ትልቅ በሆነው በጎነቱ የሰውን በደል ይቅር እንደሚል ተስፋ ይሰጣል፡፡
በተለያዩ የእምነት ክፍሎች ይቅርታ ትርጉም አለው፡፡ በዓለም ዙሪያ ብዙ የእምነት ዓይነቶች መኖራቸው የሚታወስ ሲሆን አንዱ የሚያምንበት ቅዱስ መጽሐፍ ከሌላው መጽሐፍ ይለያያል፡፡ ለምሳሌ የክርስትና እምነት በመጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ግን ስለይቅርታ የሚያስተምረው ሰዎች በዓለማዊ ልማድ ከመሰረቱት ይቅርታ እጅግ የሚለይ ነው፡፡ ስለ ይቅርታ ከቃሉ የምንማረው እውነት በሥራ ላይ ለማዋል የውስጥ ጥንካሬንና መንፈሳዊ ቁርጠኝነንም ይጠይቃል፡፡
እስልምና ደግሞ በቁርዓን ላይ ሲያምን የተመሠረተ ነው፡፡ ታዋቂዎቹ የእምነት ክፍሎች እነዚህ ቢሆኑም ቡድሃ፣ ሕንዱ ጃይኒዝም፣ የአይሁድ ሃይማኖት ደግሞ የየራሳቸው የእምነት አቋም ያላቸው ናቸው፡፡ እነዚህ እያንዳንዳቸው ስለይቅርታ የሚሎት አላቸው፡፡
ለምሳሌ አንድ ጥፋት ሰርቶ እንደሆነ ይቅርታን መጠየቅ የሂንዱ እምነት ልምምዶች ከሆኑት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ በእስልምና እምነት መሠረትም ቢሆን አምላክ/አላህ/ የይቅርታ ሁሉ ምንጭና ይቅር ባይ ነው፡፡ ይቅርታን የሚፈልግ ሰው ንስሐ ሊገባ ያስፈልገዋል፡፡ ሰዎች ንስሐ ሲገቡ ከአላህ ዘንድ በቀጥታ ይቅርታ ይደረግላቸዋል፡፡ ከእግዚአብሔር /ከአላህ/ ይቅርታን ለመቀበል ሶስት ነገሮች ማሟላት አለባቸው አንደኛው የሰሩትን በደል ማወቅና በእግዝአብሔር ፊት ማቅረብ ሁለተኛው ያንኑ በደል ደግመው ላለመስራት መወሰን ሲሆን ሶስተኛው ከእግዚአብሔር ይቅርታን መጠየቅ ነው፡፡
በጃይኖች እምነት መሠረት ደግሞ አንድ ሰው ይቅርታን ለማግኘት ከተለያዩ ፍጥረታት ደጋጋሞ ይቅርታ ከትንንሽ ፍጥረታትና እጽዋት ሁሉ ይቅርታን መጠየቅ ይጠበቅበታል፡፡ ይቅርታ የዚህ እምነት ተከታይ መሆን የፈልግ ሰው ከሚከተላቸው አብይት ተግባራት አንዱ ነው፡፡ በአይሁድ እምነት መሠረት አንድ ሰው በሌላው ላይ በደል አድርሶበት ከሆነ ወደ ተበደለው ወገን ሄዶ ይቅርታ መጠየቅ አለበት፡፡ የራሱን ግዴታ ለመወጣት ስለ ሠራው በደል ሶስት ጊዜ ይቅርታን መለማመን ይኖርበታል፡፡ እነዚህ ለምሳሌ ያህል የምንመለከታቸው ሲሆኑ ይቅርታ በሁሉም አንፃር እንዴት የከበረና በጥብቅ የሚፈለግ ሃይማኖታዊ ማህበራዊ እይታን የሚስብ እንደሆነ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡ ማንኛውም ይሁን ለሰው የሚደረግ ይቅርታ የሚሰማውን ሁሉ ያስደስታል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ግን ስለ ይቅርታ የሚያስተምረው ሰዎች በዓለማዊ ልማድ የመሰረቱት ይቅርታ እጅግ የሚለይ ነው፡፡ ስለይቅርታ ከቃሉ የምንማረው እውነት በሥራ ላይ ለማዋል የውስጥ ጥንካሬንና መንፈሳዊ ቆራጥነትንም ይጠይቃል፡፡ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት አንባቢያን የነበሩ አይሁዶች ስለይቅርታ ጥልቀት ያለውን ግምት የሚሰጡ ሲሆን በእነርሱ አተረጎጎም መሠረት ይቅርታ ማለት መሸከም፣ መታገስ ወልወል አድርጎ ማጽዳት፣መሸፈን ማለት ነው፡፡ የብሉይ ኪዳንን መጽሐፍት ወደ ግሪክ ቋንቋ የተተረጎመ ሴኘቱኤጀንት ተብሎ የሚታወቀው የሰባ ሊቃውንት ጉባኤ በተረጎመው መሠረት ከሆነ አፒ.ኤሚ፣ዴኮማይ፣ኢፖሪዮ፣ ሄሊዩስ ፣አይናዳ፣ ኤክስልዮስኮማይ የሚባሉና ከእነዚህ ጋር ተቀራራቢነት ያላቸው የተለያዩ ቃላት ስለይቅርታ በጥልቀት ያስረዳሉ፡፡ ምን ማለት እንደሆነ ተብሎ ሲጠየቅ ይቅርታ ማለት፣ ማስወገድ፣ መማር፣ ማጽዳት፣ በአድናቆት የመቀበል ግንዛቤ ማሳየት የሚለውን የሚያሳዩ ናቸው፡፡
በአዲስ ኪዳን ይቅርታ ጥልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን በእግዚአብሔር ቃል እንደምናምን ክርስቲያኖች እንደሚተለው የተቀመጡትን ሐሳቦችን መተርጎም ይገባናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ፡፡
በእግዚአብሔር ባህሪይ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
እግዚአብሔር በባህሪው ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ ነው፡፡ የመረጣቸውና የጠራቸው የእስራኤል ሕዝቦች ደጋግመው ሲበድሉ ይቅርታ ሊላቸው አልሰለቸውም፡፡ በአባትነት ምክር ቢገስፃቸውም ተመለሰው ምህረት ሲለምኑት ከጠላታቸው እያዳናቸው ቃል ኪዳኑን ሳይረሳ ይቅርታውንና ምህረቱን ለሺህ ትውልድ የሚጠብቅ አምላክ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆላስይስ ቤ/ክ አማኞች በተፃፈው መልዕክት እርስ በእርሳቸው ይቅርታ እንዲባባሉ ይመክራቸዋል፡፡ ይህንን ማድረግ የሚችሉት ክርስቶስ ያደረገላቸን ሲያስቡ ብቻ ነው፡፡ " ማንም ባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው ይቅርታ ተባባሉ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተም ደግም ይቅርታ ተባባሉ" ቆላ 313፡፡ ከእግዚአብሔር የምንማረው ባህሪያቱን ነው፡፡ እርሱ ፍቅር እንደሆነ ፍቅርን እንድንለማመድ እንደሚጠበቅብን ሁሉ የቅርታንም ከእርሱ እንማራለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ክርስቲያናዊ ይቅርታ በክርስቶስ ባህሪይ በሆነ የይቅርታ ሥራ ላይ የቆመ ነው፡፡ ያለዚያ እውነተኛ ይቀርታ የለም፡፡ የእግዚአብሔርን ይቅርታ የምንቀበልበት መንገድ ነው፡፡ የክርስቶስ ፍቅር ከሁሉም በላይ በመሆኑም የበደሉንን ይቅር ከማለት አልፎ በፍቅር መቀበል የእውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ መገለጫ ነው፡፡ ይቅር ብያለሁ ማለት ብቻውን አይበቃም፡፡ መቀባበልና መውደድ ይቅርታን እውነት ያደርገዋል፡፡ ማቴ 614
የምንኖረው ከሰዎች ጋር ሲሆን እያንዳንዱ ሰው ደግሞ ኃጢአተኛ ስለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለንም፡፡ ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር እንድንል ታዘናል፡፡ ይቅር የምንለው ኃጢአተኛው የቱ ነው? የውርስ ኃጢአታቸው ወይስ የድርፍረት ኃጥአታቸው ? እንዲህ አይነቱን ይቅር ማለት የሚችል ከእግዚአብሔር ሌላ አይኖርም፡፡ ታዲያ ይቅር እንድንላቸው የተጠየቅነው ከእኛ ጋር በተያያዘ ያስቀየሙንንና ያሳዘኑንን በደላቸውን ከውስጣቸው አውጥተን ስለመጣል እንጂ፡፡ ከሚወዱት ሰው መጎዳት በሚያውቁት ሰው መጠቃት ልብን ያሳዝናል፡፡ እንደዚህ ባለ ወቅት በደልና ኃጢአት መልሰን ከመቁጠር ይልቅ ምህረት እንድናደርግ ታዘናለ፡፡ ይህንን የሚመስል ልምምድ ሲኖር ከእግዚአብሔር ይቅርታን እናገኛን፡፡ ሰዎች ይበድሉናል እኛም ደግሞ በራሳችን አቅጣጫ እግዚአብሔርን እንበድለዋለን፡፡ ምህረት ካልተደረገልን የሚጠብቀን የእርሱ ቁጣ ነው፡፡ እርሱ ይቅርታ እንዲለን የምንፈልግ ከሆነ መንገዱ ለሌሎችን ይቅርታ ማለት ብቻ ነው፡፡
በኃጢአታችን ጊዜ ምህረትን በህመማችን ወቅት ፈውስን በችግራችን ጊዜ እርዳታን ከጌታ እንጠብቃለን፡፡ የምንፈልገውን ስናገኝ አብዝተን ደስ እንሰኛለን፡፡ ጌታም የምንፈልጋቸውን ሁሉ የሚያደርግልን መልካምነታችን ማርኮት ሳይሆን ብዙ በሆነው ምህረቱና ይቅርታው ምክንያት ነው፡፡ እኛም የበደሉንን ሰዎች በደል ከልባችን በማውጣት ኃጢአታቸውን በማስወገድ ልባችንን በማንፃት እነርሱን ፈጽመን ለመቀበል ዝግጁ መሆን ይጠብቅብናል፡፡ በባህሪያችን መስጠት እንጂ መቀበል አያቅተንም፡፡ ምህረትና ይቅርታን ስንቀበል እንደሰታለን ጨምረንም እንመኘዋለን፡፡ ለሌሎች ይቅርታን ለማድረግ ግን ይከብደናል፡፡ ስለዚህ ነው ይቅርታን በማድረግ ወቅት ስሜታችንን የጎዱንን ይቅር ብለን መባረክ መንፈሳዊ አቅምንና የውስጥ ቆራጥነትን የሚጠይቅ ነው ያልኩት፡፡ በየትኛውም መንገድ ቢሆን ከእግዚአብሔር ይቅርታን የመንቀበለው የሰዎችን በደል ይቅር ስንል ብቻ መሆኑን ቃሉ በግልጽ ያስተምረናል፡፡
በደለኛውን በምህረትና በፍቅር መቀበል ነው፡፡
ይቅር ብሎ መተው ብቻ ሳይሆን በፍፁም ምህረትና በይቅርታ መንፈስ የራስ አድርጎ በፍቅር መቀበል ነው፡፡ መቀበል የሚለው ቃል እንዲሰመርልኝ እፈልጋለሁ፡፡ እንዲህ አይነቱ አባበልን ዕብራውያን/Dechomai/ ዴኮማይ ብለው እንደሚጠሩት አዲሱ የሥነ-መለኮት መዝገብ ቃላት /the new dictionary of biblical theology/ ይነግረናል፡፡ የበደሉንን ሰዎች ኃጢአትና በደል ይቅር ማለት ብዙም ላይከብደን ይችላል፡፡ ነገር ግን እነርሱን እንደ አካላችን አድርገን መቀበል አቅምን የሚፈታተን ነው፡፡ የቱም ቢሆን የእግዚአብሔር ሐሳብ ይኸው ነውና ማድረግ ይኖርብናል፡፡
ጊዜው በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ1992 .. ገደማ ነው፡፡ የተወሰኑ አይሁዳዊያን ለጉብኝት ወደ አገራችን መጥተው ነበር፡፡ ቁጥራቸውም ወደ ሃያ የሚጠጋ ሲሆን ወንዶችም ሴቶችም በዕድሜአቸው የገፋም ደግሞ ወጣቶችም ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሰዎች እኔ በማገለግልበት ቤተክርስቲያን በአንድ ምሽት ምስክርነት እየሰጡ ያጽናኑና ያስደንቁ ነበር፡፡ የአንዲት ባልቴት ምስክርነት ግን ምን ጊዜም ከልቤ ሊጠፋ አልቻለም፡፡ እንዲህ አሉ የናዚ ጀርመን አይሁዶችን በጨፈጨፈበት ወቅት እኔ ቢበዛ የሶስት ዓመት ልጅ ነበርኩ፡፡ በአንድ ሥፍራ ከሴት አያቴ ጋር እያለን የናዚ ወታደሮች መጡብን፡፡ ልጅ ስለነበርኩ ስለጉዳዩ ምንም ግንዛቤ አልነበረኝም፡፡ ግን ወዲያው አንድ አሰቃቂ ነገር ተፈጠረ ፡፡ ያውም አያቴን በፊቴ ሰውነቷን እየቆራረጡ በታትነው ሥጋን እንኳን መለየት እስከማይቻል ድረስ አበላሽተው ከገደሏት በኋላ እኔ ምርር ብደ እያለቀስኩ ብቻዬን ትተውኝ ሄዱ፡፡ የነበረው የአገዳደል ሁኔታ በአህምሮዬ ተስሎ ያሰቃየኝ ጀመር፡፡ በኋላ ሰዎች አግኝተውኝ ወስደው አሳደጉኝ፡፡ ቤተሰቦቼ ሁሉ በተመሳሳይ ጭፍጨፋ አልቀው ስለነበር ያለዘመድ አደግሁ፡፡ ካደጉህ በኋላ ኢየሱስን አምኜ ከመጽሐፍ ቅዱስ የበደሉንን ይቅር ማለት እንዳለብን የሚያስተምር ቃል ሳነብ ማንንም ቢሆን ይቅር ማለት ይቻላል፡፡ ጀርመኖችን ግን እንዴት ይቅር ማለት እችላለሁ? እንኳን እኔ እግዚአብሔር እንዴት ይቅር ይላቸዋል? ብዬ እሟገት ጀመርኩ፡፡ በኋላ ግን ይህንን ካላደረኩ እኔንም እግዚአብሔር ይቅር እንደማይል በቃሉ ስለተናገረኝ በፍፁም ልቤ ይቅርታ አልኩ ብለው መሰከሩ፡፡ እኚህ እናት በምስክርነታቸው ከተናገሩት ከባድ ነገር ይቅር ብለው ማለፍ የሚቻል ቢሆንም ጀርመኖችን መውደድስ ይቻላልን? ማለታቸው ነው፡፡ የክርስቶስ ፍቅር ከሁሉም በላይ በመሆኑ የበደሉንን ይቅር ከማለት አልፎ በፍቅር መቀበል የእውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ መገለጫ ነው፡፡ ይቅር ብያለሁ ማለት ብቻውን አይበቃም፡፡ መቀባበልና መውደድ ይቀርታውን እውነት ያደርገዋል፡፡ ለዚህ ዋቢ የሚሆነን አንድ ምሳሌ ማየት ይጠቅመናል፡፡
አንደኛው በዘፍጥረት 5017 ላይ የምንማረው ታሪክ ሲሆን በወንድሞቹ የተበደለ ዮሴፍ እግዚአብሔር ታሪኩን ለውጦለት በዳዮቹን በእጁ በጣለለት ወቅት ያዕቆብ ይቅር በላቸው ብሎ መልዕክት ላከለት፡፡ እነርሱ ከፈተውብሃል፣ ግን የአባትህ አምላክ ባሪይዎች ናቸውና ይቅር በላቸው ሲለው መልዕክቱን ሰምቶ አለቀሰ፡፡
የያዕቆብ ልጆች ተባብረው ወንድማቸው በሆነው በታናሹ ዮሴፍ ላይ እጅግ የሚያሳዝን በደል አድርሰውበታል፡፡ "እባክህ የወንድሞችህን በደለ ኃጢአታቸውንም ይቅር በል እነርሱ በአንተ ላይ ከፍተውብሃል የሚለውን የአባታቸውን መልዕክት ተቀበለ፡፡ በሌላ አባባል ወንድሞችህ ክፉ አድርገውብሃል ስለዚህ ይቅር በላቸው የሚለው የአባቱ የይቅርታ ጥሪ ዮሴፍ የተቀበለው በእምባ ነበር፡፡ ቃሉ አለቀሰ ይለናል፡፡ ይህ ልቅሶ የቂም በቀለ ልቅሶ ሳይሆን ወንድሞቹን ለመቀበል ያደረገው ልቅሶ ነበር፡፡ ክፋት ያደረጉብንን ክፋም ሆነውብን ስንለምናቸው እንኳን አንሰማ ብለው በጭካኔ የልባቸውን ሐሳብ የፈፀሙብንን ሰዎች ቀናት ተለዋውጠው ጊዜም መጥቶ በእጃችን ወድቀው ብናያቸው ምን እናደርጋቸው ይሆን? ከእምባና ከለቅሶ ጋር ተቀብለን ምህረት እናድርግላቸው ይሆን? ወይስ በውስጣችን የታመቀውን በቀልና የቂምን ትኩሳት እናፈስባቸው ይሆን? አንድ ቀን እኛ አቅም አግኝተን እነርሱን ለመርገጥ የምንችልበት አጋጣሚው ቢሰጠን እነርሱም በእጃችን ቢወድቁ ማረን ብለው ቢለምኑን ብናይ ዓይን ለዓይን እጅም ለእጅ ሳንል በክርስቶስ በሆነው ምህረት አድርገን እንቀበላቸው ይሆን? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ የምንለው ይኸው ነው፡፡ እኛም እውነተኛ የኢየሱስ ደቀመዛሙርት የሚያሰኘን መለያችን ይህ ነው፡፡ ወንድሞቹ በዮሴፍ ላይ ያደረጉት ግፍ ከልብ የሚወጣ ከአህምሮም የሚፋቅ አልነበረም፡፡ ያኔ በትንሽ አቅሙ ሲማጠን አንሰማ ብለው ሊገድሉት ፈልገው በታላቅ ወንድማቸው ጣልቃ ገብነት ሐሳባቸውን ቀይረው ራቁቱን በጉድጎድ ውስጥ ጥለው ከዚያም አውጥተው እንደ በግ ጠቦት በትንሽ ዋጋ ሸጠው ያንከራትቱት ጨካኞች የእግዚአብሔር ቀን መጣና በእርሱ እጅ ሲወድቁ በዓይኑ አየ፡፡ ብድራታቸውን ለመክፍል አሁን ቀኑ ደርሷል፡፡ ለሰሩት ክፉ ሥራ ሰባት እጥፍ የሚያስከፍልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ይሁን እንጂ ክፋ አድርገውብሃልና ይቅር በላቸው ሲባል ይቅር ማለት አልከበደውም፡፡ ያውም ከአምባ ጋር፡፡ ይህ እውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ ነው፡፡
በእርግጥ ሕይወታችንን ስንመረምረው ከዚህ አንፃር ምን ይመስላል? እንዲያው የበደለንን ሰው በፍቅር እንቀበለው ይሆን? ይቅርታ አድርጉልኝ ብሎ ሲመጣ አይተናል ከእምባ ጋር እንቀበለው ይሆን?
አባካኙን ተቀብሎ የሚሸከም ነው፡፡
በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 የምንመለከተው የአባካኙ ልጅ አባት የሰራው ሥራ አስደናቂ ነው፡፡ ልጁ እኮ ከአባቱ ሐብት ምንም ድርሻ ላይፈልግ የሚገባውን ወስዷል፡፡ ካደረጋቸው ከባድ በደሎች አንዳንዶቹ እንጥቀስ፡-
አባቱ በሕይወት እያለ ድርሻ መጠየቁ በኢትዮጵያውያንም ዘንድ ቢሆን በጣም አስነዋሪ ተግባር ሊባል ይችላል፡፡ በአይሁዶችም ባህል ቢሆን እንዲህ ዓይነቱ ልማድ የላቸውም፡፡ የራሱ ያልሆነውን ግን የአባቱን ገንዘብ ወስዶ ወደ ሩቅ አገር ሄዶ አባከነ፡፡ ያም ባለፋ እሪያዎች ከሚበሉት አሰር ለመጥገብ ተመኘ፡፡ በእስራኤል ልጆች አሳማ/እሪያ/ እንደ እርኩስ የሚቆጠር እንስሳ ነው፡፡ ያንን የመሰለ ሕይወት ለመኖር ራሱን አሳልፎ ሰጠ፡፡
ገንዘቡን ያባከነው ከጋለሞታዎች ጋር ነው፡፡ እነዚህ ከበደለኝነትም ከባድ በደለኝነት ተደርጎ ሊቆጥሩ ይችላሉ፡፡ እኛ አባት አብርሃም አለን ብሎ ከሚመፃደቅ ማህበረሰብ መካከል የተወለደ ልጅ እንደዚህ አይነት ሥራ መስራቱ ለወላጅ አባቱ የልብ ስብራት ሊሆን ይችላል፡፡ ቢሆንም ልጁ አባቱን ልጅህ ልሆን አይገባኝም፡፡ ከሞያተኞች እንደ አንዱ አድርገኝ ብሎ ለመለመን ሲመጣ አባትየው ከሩቅ አይቶ አዝኖለት አቅፎ በመሳም ምንም ጊዜ አልፈጀበትም፡፡ ለእግሩ ጫማ ለጣቱ ቀለበት እንዲያውም የሰባ ፍሪዳ አርዶ አብረው ለመደሰት አልከበደውም፡፡ ከዚህ ለጅ አባት የምንማረው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታን ነው፡፡ አባካኙን የሚሸልም ነው፡፡ ለእግሩ ጫማ ለጣቱ ቀለበት የሚያመጣ ያውም የሌሎችን ተቃውሞ ወደ ጎን ትቶ ፡፡
ቀጠሮ የማይሰጥ ሉቃስ 2334
ይቅርታ ለመስጠት ጊዜ መውሰድ አያስፈልግም፡፡ ብዙ ጊዜ አማኞች ሕይወት የምናየው የቅዱስ ቃሉ ከሚያስተምረን ውጭ ነው፡፡ በደልንና የልብን ሐዘንን ተሸክመው አስታራቂ ይፈልጋሉ፡፡ በመሠረቱ አስታራቂ የሚያስፈልገው መግባባት ሲያቅት ወይም ሁለት ወገኖች እርስ በእርሳቸው እንደጠላት የተያዩ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን አስታራቂ እስኪመጣ ሳይጠብቁ በደለኛውን ይቅርታ ማለት ይቻላል፡፡ ይቅርታውን እውነተኛ መጽሐፍ ቅድሳዊ የሚያደርገው ይህ ነው፡፡ ኢየሱስ ይቅር ያለን በእርሱና በእኛ መካከል ምንም አስታራቂ ሳይፈልግ ነው፡፡ ጌታ በመስቀል ላይ የሰቀሉትን የሮማውያን ወታደሮችን እዚያው ይቅርታ አድርጎላቸዋል፡፡ በመስቀል ከመስቀላቸው በፊት የገረፋትን፣ እንጨት አሸክመው እየገፈታተሩ ወደ ዳገት ያራመዱትን የሮማውያን ወታደሮችን ከባዱ የእንጨት መሸከም ሥር ሆኖ እየተንገዳገደና እየተደናቀፈ ሲወድቅና ሲነሳ እያዩ ያልራሩለትን በጥፊ እየመቱት ሕጋቸው ከሚፈቅደው በላይ በደል ካደረሱበት በኋላ በመስቀል ላይ መስቀላቸው ሳያንስ መራራ ውሃ ያጋቱትን የሮማውያን ወታደሮችን ይቅርታ ለማለት ጊዜ አልፈጀበትም፡፡ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ያለው እዚያ በመስቀል ላይ ሆኖ ነው፡፡ ልብሱን ሲከፋፈሉ አይቶ፡፡
ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስም በመልዕክቱ ውስጥ ተቆጡ. . . በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፣ ለዲያቢሎስም ፈንታ አትስጡ፡፡ ኤፌ 426 ያለው ስለዚህ ነው፡፡ ቂምና ቅሬታ ውሎ ማደር የለበትም፡፡ ውሎ ቢያድር ተበዳዩም አይጠቀምበትም በዳዩም አይጎዳበትም፡፡ ዲያቢሎስን ከማስደሰት ሌላ የሚፈይደው ነገር አይኖረውም፡፡ መጽሐፍ ቅድሳዊ ይቅርታን ከሌሎች የተለየ የሚያደርገው ይህ ነው፡፡ ተበድያለሁ ተጎድቻለሁ የሚለው ሰው ምንም ጊዜ ሳይሰጥ ባልንጀራውን ይቅር ማለት ይኖርበታል፡፡ እየሰደበ፣ በጥፊ እየመታ ፣ ስብዕናችንን እየጎዳ በሞራላችን ላይ እየተረማመደበት እያለ በዚያው ሰዓት ወንድማችን ነውና ይቅር ማለት ይቻል ይሆን? ኢየሱሱና እስጢፋኖስ ያደረጉት ይህንን አይደል? ኢየሱስ ጎኑ በጦር እየተወጋ እያለ እስጢፋኖስ ተኝቶ በድንጋይ እየተወገረ እያለ ስለጠላቶቻቸው ሕይወት ከአብ ዘንድ ይቅርታን ለምነዋል፡፡ ዛሬ በቤተክርስቲያን የሚታየው ግን የዚህ ተቃራኒ መሆኑ አሳዛኝ ነው፡፡ ታረቁ ብለው የሚሰብኩ ታላላቅ የቤተክርስቲያን መሪዎች ይቅርታ ለማድረግ ሁለትና ሶስት ዓመታት ከዚያም በላይ ሸንጎ ካልተቀመጠ እሺ አይሉም፡፡ የአንዳንዶች ችግር የሚፈታው በይቅርታ መንገድ ሳይሆን የውጭ አይላት ጣልቃ ሲገቡ ነው አሳፊሪ!!፡፡ ይህ ለክርስትና ምን ያህል ሩቅ መሆናችንን የሚያሳይ ነው፡፡ የብዙ ቤተክርስቲያን መሪዎች መጽሐፍ ቅዱስ የሼልፋቸው ማዳመቂያ እንጂ በእርግጥ የሚያምኑበት አይደለም፡፡ ለዚህ ብዙ ማስረጃ መቁጠር ሳያስፈልግ ወንድማቸውን ይቅር ማለት አቅቷቸው ልበ-ቅን ምዕመናን የሚያስለቅሱበትና የሚጎድበት ሕይወታቸው በቂ ነው፡፡
ቀጣይት ያለው ነው ፡፡ ማቴ 1821-22
ለመሆኑ እኔ ወንድሜን ይቅር ማለት ያለብኝ ስንት ጊዜ ነው? ከወህኒ የተፈቱ ወንጀለኞች ያንኑ የቀድሞ ጥፋታቸውን እንዳይደግሙት መጠንቀቅ አለባቸው፡፡ በሌላ ወንጀል ቢጠረጠሩ ወዮላቸው ሪከርድ አላቸውና ቅጣታቸውም ሊከብድ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ግን ከዚህ ይለያል፡፡ ወንድማችን ደጋግሞ ቢበድለን ደጋግመን ይቅር እንድንለው ቃሉ አዞናል፡፡ ወንድሜ ሰባት ጊዜ ቢበድለኝ ሰባቱንም ጊዜ ይቅር እላለሁ? ብሎ ጴጥሮስ ለጠየቀው ጥያቄ ኢየሱስ የመለሰው መልስ አስፈሪ ነው፡፡ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ ሰባት ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ለመሆኑ አንድ ሰው ያንኑ ያህል ይበድለኛል? አይመስለኝም፡፡ ጌታ እንዲህ ያለውን ምን ጊዜም ቢሆን ደጋግሞ ይቅር ማለት እንደሚገባን ለማመልከት ነው፡፡ እንደክርስቲያን ባለፈው ይቅር ያልነው በደል አሁን አይታሰብም፡፡ የዛሬው ጉዳይ ዛሬ ብቻ መታየት ይገባዋል፡፡ ዛሬ ተበድሎ ትናንት ይቅር ያለውን በደል የሚቆጥር ሰው ከልቡ ይቅር አላለም ነበር ማለት ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረገ ይቅርታ ወዳጃችንን ሁልጊዜ ይቅር ማለት ነው፡፡ እባካችሁ ይህንን ጽሑፍ የምታነቡ ወገኖች ሁላችሁም ለባልንጀራችሁ ይቅርታ ያደረጋችሁላቸውን ጊዜያቶች አትቁጠሩ፡፡ በልባችሁም እርሱን መዝግባችሁ አትያዙ፡፡ ባልንጀራችሁ በየትኛውም ጊዜ ይቅርታ አድርጉልኝ ቢላችሁ ደስ እያላችሁ ይቅር በሉት፡፡
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ በዙሪያው በጣም ብዙ እንቅፋቶችና ግልጽ ያልሆኑ ጥያቄዎች አሉት፡፡ የጌታ ፍቃድ ቢሆን እነዚህን አንድ በአንድ እያነሳን እንመለከታለን፡፡
ይሸፍናል፡፡ ስለዚህ ዓለማዊውን ሰው ቢሆን ይቅር ማለት ይኖርብናል፡፡
በክፋ ፋታ ክፋን አትመለስም ሮሜ 1217
በጎችና ውሾች በጣም የተለያዩ ፍጥረቶች /እንስሳት/ ናቸው፡፡ ውሾች መጥፎዎች አንዳንዴም ተንኮለኞች ናቸው፡፡ ከዱር አውሬ የከፋ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ውሾች አሉ፡፡
ውሻ የሚፈራ በጣም ብዙ ሰው አለ፡፡ በጎች ደግሞ ተንክል የሌላቸው በየዋህነታቸው የሚታወቁ የቤት እንስሳት ናቸው፡፡ ውሾችና በጎች በአንድ አካባቢ የሚኖሩ ቢሆንም ውሾች በበጎች ላይ ይጮሃሉ፡፡ የቱንም ያህለ ቢጮሁ በጎች መልሰው ውሾች በጮሁበት አጯጯህና ድምጽ ውሾች ላይ አይጭሁባቸውም፡፡ ምክንያቱም የተሰጣቸው ባህሪይ ስለማይፍቅድ እንዲሁም ሁሉ ከክርስቶስ የተማርነውና የተቀበልነው መልካም ማንነታችን ክፋን በክፋ መመለስ አያስችለንምና፡፡ ለማንም ስለክፋ ፋንታ ክፋ አትመለሱ ይላል፡፡ ለማንም ሲል ምን ማለቱ ነው? ዓለማዊው ያላመነው ሰው ክፋ ቢያደርግብን እኛ ክፋን ለእርሱ መመለስ አይኖርብንም፡፡ አማኝ ወንድማችንን ክፋ ቢያደርግብንም በክፋ ፋንታ ክፋ አትመልሱ ብሎ አያበቃም፡፡ በሰው ሁሉ ፊት /ባመኑም ባላመኑም/ ፊት መልካም የሆነውን እንድናስብ ይጠየቀናል፡፡ የክፋ ሥራ መነሻ የሚሆነው ክፋ ሐሳብ እንደሆነ አያራጥርም፡፡ በመልካም ሐሳብ የተሞላ ሰው ድርጊቱ መልካምና በጎ ይሆናል፡፡ ይህም በመሆኑ አለማዊውን ሰው ይቅር ብለን ምህረት እንድናደርግ የእግዚአብሔር ፍቃድ ነው፡፡
እናንተ አትበቀሉ፡፡ ሮሜ 1218-19
አማኞች እንዳንበቀል የሚያደርጉ ሁለት ታላላቅ ምክንያቶች አሉ፡፡ አንደኛው ተወዳጅነታቸው ነው፡፡ ለአማኞች ከተሰጣቸው ደማቅ ስሞች አንዱ ይህ ነው፡፡ ተወዳጅነታችን በእግዚአብሔርም በሰውም ፊት ከሆነ ማንንም ለመቀበል ጉልበት እናገኛለን፡፡
ሁለተኛው የበደሉን ሁሉ ብድራታውን ይቀበላሉ በቀልም የጌታ ነው፡፡ በቀል ቢያስፈልግም ጌታ እንዲቀበልና ብድራቱን እርሱ እንዲመልስ ዕድል ፈንታ ለጌታ እንድንሰጥ ጳውሎስ ጠይቆናል፡፡ የበቀሉን ጉዳይ ለጌታ መተው ይሻላል፡፡ እግዚአብሔር እናንተ አትበቀሉ እኔ ግን እበቀላለሁ ይላል ተብሎ እንደተፃፈው የሚያስታውስ ሲሆን በቀል ማለት በሌላ አገላለጽ ቅጣት ማለት ነው፡፡ መቼም ቢሆን ጌታ ሳይበቀልልን አይተውም፡፡ ዘመናት ይረዝሙ ይሆናል ወይም እርሱ የረሳን አድርገን እንቆጥር ይሆናል እንጂ ለእያንዳንዱ ብድራቱን ሳይመልስ አይቀርም፡፡ የሰው ልጅ ከመላዕክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንደ አለውና ያን ጊዜ ለሁሉም እንደሥራው ያስረክበዋል፡፡ ማቴ 1627 ክፋን ያደረገ ብድራቱን መቀበል እንዳለበት በእርግጠኝነት እናምናለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ቢሆን ክፋ አድራጊው በዚያው ድርጊቱ እንዲቀጥል ተፈቅዶለታል እያለ አይደለም፡፡ እያንዳንዱ የሥራውን ዋጋ ይቀበላል ይለናል፡፡ ይሁን እንጂ ክፋ ላደረጉብን ሰዎች ከሥራቸው ጋር የተመጣጠነ ምላሽ መስጠት የእግዚአብሔር ጉዳይ ነው እንጂ የእኛ አለመሆኑን ያስገነዝበናል፡፡
ጠላቶቻችሁን አገልግሉ፡፡ ሮሜ 1220
"ጠላት ቢራብ አብላው ቢጠማም አጠጣው" በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ የተስፋ ቃሎች፣ ምክሮች ተግሳፆች እና ትህዛዞች አሉ፡፡ ሁሉንም የእኛ እንድናደርጋቸው ይፈልጉብናል፡፡ በተለይም ደግሞ የተስፋ ሐሳብ ያሉባቸውን ክፍሎች ስናነብ ወዲያው ተቀብለን እንደሰትባቸዋለን፡፡ ወደ ግሳፄ ሐሳቦች ስንመጣ ግን የልባችን መነቃቃት እንደ እዚያኛው አይሆንም፡፡ በተለይ የሮሜ መልዕክት 1220 በጣም የሚፈታተነን ትህዘዝ ነው፡፡ ለአንባቢያን በእርግጠኝነት የምለው አለኝ፡፡
ይህ ክፍል ባነበብኩ በመጀመሪያው ወራት መልዕክቱ ለእኔ አይደለም፡፡ የተፃፈው ብዬአለው፡፡ እርሱ ለሮሜ ቤ/ክ ሰዎች እንጂ ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ብዬ ነበር፡፡ ይህንን ያልኩበት ምክንያት ጠላቴ ሲራብ አይቼ የጣፈጠ ምግብ ሲጠማም ሳይ ቀዝቃዛ ውሃ አቅርቤለት ሥጋውን መደገፈ የመችልበት አቅሙ ስለሌለኝ ማምለጫ እንዲሆነኝ ብዬ እንጂ ቃሉስ በደንብ ይመለከተኛል፡፡ እንደ እኔ አይነት የሆነ ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች አይኖሩም ብዬ አላምንም፡፡ አንዳንድ ጠንከር ያሉ ክፍሎች ሲነበብላቸው ይሄማ ለቀድሞዎቹ ሰዎች የፃፈ ነው ይላሉ፡፡ በአንድ ሥፍራ ቃሉን በጋራ እያነበብን " ሴት ለባሏ ትገዛ" በሚለው ሐሳብ ዙሪያ ስንወያይ አንዳንድ ሰዎች ይህ እኮ በኤፌሶን ላሉ ሰዎች ነው የተፃፈው፡፡ ለእኛ አይደለም ብለው ያርፋቡትን ቀን አልረሳውም፡፡ የማያወላዳ እውነት ግን ሁሉም ሐሳቦች በመጀመሪያ የተፃፋት ለእኛ አይደሉም፡፡ በጊዜው የነበሩ ፀሐፊዎች በዚህ ዘመን እንበልና በኢትዮጵናያ ያለነውን የአሁኖቹን አማኞች በጭራሽ አያውቁም ነበር፡፡ ቃሉን እንዲጽፉ ለእነርሱ የሰጣቸው ያኔ ከእነርሱ ጋር ሲሰራ የነበረው መንፈስ ቅዱስ ግን ዛሬም ቃሉን ሳይለውጥ ስላለ እኛን አይመለከተንም ለማለት አንችልም፡፡ ስለዚህ ከማንነታችን ጋር የማይመስል ቢሆንም ከቃሉ አንድንም ሳናስቀር እንኖርበታለን፡፡ እንገዛለትማለን፡፡ እንግዲህ ጠላትህ ቢራብ አብላው ቢጠማም አጠጣው ማለት በአጭር ቃል የበደለህን ሰው የማያምን አለማዊ እንኳን ቢሆን በመልካም ልብ ቀርበህ አገልግለው ማለት ነው፡፡ እንደዚህ ከሆነ አለማዊያን ቢበድሉንም እንኳን ይቅር ማለት ይኖርብናል፡፡
ጠላታችን ቢራብ የምናበላው ሲጠማስ የምናጠጣው ከሆነ ውጤቱ መን ይሆናል? ብለን ባናልፈው ጥሩ ነው፡፡ " ጳውሎስ እንዲህ አለ ይህንን በማድረግ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህ" ይለናል፡፡ በጠላታችን ራስ ላይ የእሳት ፍም መከመር ማለት ምን ማለት ነው? ለዚህ መልስ እንዲሆን የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኞች የሚያቀርቧቸው የተለያዩ አማራጭ ትርጉሞች አሉ፡፡
አንደኛ- በበደለኛው ላይ የእግዚአብሔር ቅጣት ጠንከር እንዲል ማድረግ ነው፡፡ የእሳት ፍም የፍርድ ወይም የቅጣት ምልክት ነው፡፡ ወጥመድ በኃጢአት ላይ ይዘንባል፡፡ እሳትና ዲን አውሎ ነፋስም የጽዋቸው ዕድል ፈንታ ነው፡፡ መዝ 116
ሁለኛው ደግሞ በደለ ያደረገብንንም ሰው ማሳፈር ነው፡፡ የእሳት ፍም በክፋ ፈንታ መልካም ስናደርግላቸው በደለኞች የሚሰማቸው ሐፍረት ወይም የመሸማቀቅ ምሳሌ ነው፡፡ እኔ ያንን ያህል ክፋ ነገር እያደረኩበት እንደዚህ መልካም ያደርግልኛል ብሎ በሠራው ሥራ እንዲፀፀት ማድረግ ነው፡፡
ሶስተኛው፡- አማራጭ ንስሐ እንዲገባ ማድረግ ነው፡፡ በጥንት ዘመን በግብፆች ልማድ መሠረት አንድ በደል የሰራ ሰው ከሰራው በደል ንስሐ ሲገባ እሳት ፍም በአናቱ ላይ ተሸክሞ እንዲሄድ ይደርጋል፡፡ ይህንን በሚያደርግበት ወቅት ንስሐ መግባቱንና በኃጢአቱ መፀፀቱን ያሳያል፡፡ እንደዚሁ እኛ የምንሰራው መልካም ሥራ በደለኛው በበደሉ ተፀጽቶ ንስሐ እንዲገባ ያደርገዋል ማለት ነው፡፡ መልካም ማድረግ የበደለኞችን ልብና አህምሮ በንስሐ ወደ መመለስ ይመራዋል ማለት ነው፡፡ ሶስቱን ሐሳቦች አከብራቸዋለሁ፡፡ ዓለማዊው ሰው ቢበድልህ ይቅር እላለሁ ወይ? ለሚለው ሐሳብ ከብዙ ነጥቦች ጥቂቶቹን ተወያያተንበታል፡፡ ለጊዜው በዚሁ ገና እናድርግና ወደሚቀጥለው እንለፍ፡፡
አውቆ የልቡን ከፈፀመ በኋላ ይቅርታ አድርግልኝ ቢል ላድርግለት ወይ?
ሁላችንንም የሚቸግረን ይህ ነው፡፡ የሚሰራው ሥራ ልክ እንዳይደለ በትክክለ እያወቀ ጉዳት ካደረሰብኝ በኋላ ይቅርታ የሚጠየቀንን ሰው እሺ ምህረት ይሁንልህ ብዬ እግዚአብሔር ያስገድደኛልን? ብለን ራሳችን የፍርዱን ውሳኔ እንሰጣለን፡፡ በእርግጥ የአንዳንድ ሰዎች ድርጊት ለይቅርታ ያለንን መንፈስ ያበላሻል፡፡ የሚሰራው ሥራ በሌላው ላይ በደል እያደረሰበት እንደሆነ የማያውቅ የለም፡፡ አህምሮውን የለቀቀ ሰው ካልሆነ ማንም ሰው ጥፋቱን ያውቃል፡፡ ቀለል ያለ የአህምሮ ሕመም ያለባቸው ሰዎች እንኳ አሉታዊ ድርጊቶቻቸውን ያውቃሉ፡፡
ሳያውቁ ኃጢአትን ቢያደርጉ በደል ቢፈጽሙ ልንኮንናቸው በድለውናል ልንላቸው አንችልም፡፡ ለምሳሌ ሕፃናት ሲሰድቡን ብንሰማ ያስቀናል እንደ አያስቆጣንም፡፡ ምክንያቱም ጥፋት ማለት የቱ እንደሆነ ወደሚለዩበት ደረጃ ገና ስላልደረሱ አንቀየማዠውም፡፡ እግዚአብሔር ኃጢአተኞች ናቸው አይላቸውም፡፡

አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል እያነበቡ ኃጢአትንና ጽድቅን እንዲለዩ ቃሉ በልባችንም በአህመሮአቸውም ቀርቧል፡" የእግዚአብሔር ቃለ የሆነው ሕግ ለሌላቸው ደግሞ ህሊናዠውም ራሱ ሕግ ነው፡፡ ሮሜ 212-16 በወገኑ ላይ በደል እያደረሰበት እንዳለ የማያውቅ ማንመ የለም፡፡ ሁሉም ሰው የሚበድለው እያወቀ ነው፡፡ ይቅርታ እንድናደርግ የምንጠይቅበት ምክንያቱመ ይህ ነው፡፡ ልቦናው እያወቀ የልቡን ስላደረሰብን የቅርታ እናደርጋለን፡፡ ሳያውቅ ቢያደርግ ኖሮ ቅር ላይለን የችላል፡፡ ሰዎዡ አንዲያውም ይህንን በደል ስላደረሰ ደስ የሰኙ ይሆናል፡፡ አንዳነዶችም ጽድቅ እንደፈፀሙ ሊቆጥሩ ይችላሉ፡፡ አንደንዶች ቀድመው የፈፀሙት በደል ሳያንስ ሌላም ለመጨመር ሊጋበዙ ይችሉ ይሆናል፡፡ በዚህ ወቅት ይቅርታ ለማድግ ኃይል አናገኝም፡፡ ቢሆንም ፍቅር የኃጢአትን ብዛት የሸፍናል፡፡ ስለተባለ ይቅርታ ማድረግ ግዴታችን ነው፡፡ ወደዚህ ደጃ ለመድረስ የእውነተኛ ደቀመዝሙርነት ሕይወት ወሳኝ መሆኑን ይ ሐሳብ ይጠቁማል፡፡ 

Wednesday, January 22, 2014

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ (ክፍል አንድ)

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ
(ክፍል አንድ)
                                                     ከፓስተር ሳሙኤል ሾንጋ

ዘመናችን ከምን ጊዜም በላይ የቴክኒዮሎጂ ምጥቀት የሚታበት እየሆነ መጥቷል፡፡ አንዱን የቴክኒዮሎጂ የፈጠራ ውጤት አይተን ሳንጠግበው ሌላው ሲመጣ ጉድ ያሰኛል፡፡ አሁን አሁንማ የሚታዩ የሰው ልጆች የፈጠራ ሥራዎች ሕይወት የላቸውም እንጂ የማያስገርሙት ሰው አለ ማለት አይቻልም፡፡ ኮምቲዩተር የተባለ መሣሪያ በሁሉም ቦታ ከመገኘቱም በላይ ወደ የሰው ቤት ሁሉ ሊገባ የሚችል ነገር እየሆነ ስለ መጣ ዶክዩሜንትና ዎርድ ስለሚባሉ ነገሮች ብዙዎቻችን እናውቃለን፡፡ አንድ የጸፍነው ወይም የምንፈልገው ሰነድ የሚቀመጠው በአብዛኛው ዶክዩሜንት በተባለው ቦታ ላይ ነው፡፡ ይህ ቦታ ሰነዶቻችንን ፊት ለፊት ልናገኛቸው የምንችልበትና ግልጽ የሆነ ቦታ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ የተቀመጠውን ፋይል ማጥፋት ይቻላል፡፡ የማንፈልጋቸውው ሰነዶች ካሉ እንዲያጠፋ ለኮምፒዩተሩ ስንነግረው ራሱ ያጠፋውና ቦታውን አጽድቶ ንጹህ ያደርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ ያንን አያስፈልግም የተባለውን ሰነድ ሪሳይክል ቢን በተሰኘው ድብቅ ቦታ ላይ ወስዶ ያስቀምጠዋል እንጂ ሙሉ በሙሉ አጥቦታል ማለት አይደለም፡፡ የኮምፒዩተሩ ባለቤት ቢፈልግ ያንን አጥፋው ያለውን ሰነድ እስቲ ልየው ቢሎ ቢያስብ ወደ ኮምፒዩተሩ ሪሳይክል ቢን ውስጥ ገብቶ እንደገና ወደ ዶክዩሜንት እንዲመለስ አድርጎ እንደ አዲስ እንደቀድሞው በአግባቡ መጠቀም ይችላል ማለት ነው፡፡ ሲፈልግ ደግሞ ወደማይታየው ሪሳይክል ቢን ወደተሰኘው ድብቅ ቦታ መልሶ ማስቀመጥ ይችላል ማለት ነው፡፡ ታዲያ ምን ጊዜም አልፈልገውም ብሎ ከቆረጠ ደግሞ ከሪሳይክል ቢንም ውስጥ አስወግድልኝ ብሎ ኮምፒዩተሩን ማዘዝ ይችላል፡፡ ያን ጊዜ በምንም ሁኔታ ሰነዱ አይገኝም ጨርሶ ከኮምቲዩተሩ ማስተዋል ተወግድዋል ማለት ነው፡፡ መልሶ ያንን ሰነድ የሚያገኝበት መንገድ አይኖርም፡፡
ከዚህ የምንማረው አንድ እውነት አለ፡፡ ከሰዎች ጋር ስንኖር አዎንታዊም አሉታዊም ጉዳዮች ሊያጋጥሙን ይችላሉ፡፡ ምንም ይሁን ምን በሚገጥሙን ጉዳዮች ተቻችለን ለመኖርና ለማለፍ መንፈሳዊ አቅም ያስፈልገናል፡፡ ራሱ ክርስትና እኮ እንደ ምንዘምረው ያህል ቀላል አይደለም፡፡ ወደ ተግባር ለመለወጥ ስናስብ የዳገት ያህል አዳጋች የእሬትም ያህል መራራ ይሆንብናል፡፡
ክርስትናን ፈታኝ የሚያደርገው አንዱ ጉዳይ የበደሉንን ይቅር እንድንል የሚጠይቀን ትዕዛዝ ነው፡፡ ይቅር ብያለሁ ማለት በጣም ቀላል ነው፡፡ ይቅር ያሉትን ጉዳይ በልብ ውስጥ ደብቀው ሳያስቀምጡ ጨርሶ ማጥፋት ግንመንፈሳዊ ጥንካሬን የሚጠይቅና የሚፈታተነን ነው፡፡ የኮምፒዩተሩ ባለቤት ሪሳይክል ቢን በተሰኘው ድብቅ ቦታ የተቀመጠውን ሰነድ ሲፈልግ እያወጣ እንደሚጠቀምበት በልባቸው ¹ዳ ደብቀው ያሰቀመጡትን ቂም ከዚያ ውስጥ እየመዘዙ እያወጡ እንደ አዲስ የሚያደርጉ ብዙ ክርስትያኖች አሉ፡፡ የረሱትንና ይቅር ያሉትን ከሪሳይክል ቢንም ውስጥ እንደሚያስወግድ ሰው ከራሳቸውም የልብ ¹ዳ ፈፅመው ማጥፋት ስላልቻሉ ራሳቸውንም ሌላውንም የሚጎዱ ጥቂት የሚባሉ አይደሉም፡፡ በአንድ ጉዳይ መግባባት አቅቶአቸው በወንድሞች አማካይነት ይቅርታ ከተጠያየቁ ዓመታት በኋላ እንኳን በሌላ ጉዳይ ቢገናኙ ያንኑ የተረሳውን እንደ አዲስ አንስተው የሚወቃቀጡ አገልጋዮችም ብዙ ናቸው፡፡
አንዳንድ ሰዎች ባልንጀራቸውን ይቅር ማለት እንዳለባቸው ያውቃሉ፡፡ እንዴት ይቅር ማለት እንዳለባቸው ግን ይቸገራሉ፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ለአገልጋዮችና ለቤተክርስቲያን ትልቅ ፈተና የሚሆኑት ይቅርታ ለማድረግ ያልተዘጋጀ ልባቸው ከሚያመነጨው ባህሪያቸው የተነሳ ነው፡፡ ስለ ይቅርታ ተገቢ እውቀትና ግንዛቤ የጎደለው ክርስቲያን በበቀልና በመራርነት የተሞላ ይሆናል፡፡ ክርስቲያኖችን ደቀመዝሙር እንዲያደርጉ የሚጠበቅባቸው ጊዜያቸውን የሰጡ አገልጋዮች እርስ በእርሳቸው በክፋት ሲፈላለጉና አንዱ በአንዱ ላይ መራራ ነገር ሲያደርግበት ሲታይ ያሳዝናል፡፡ ይቅርታ አገልጋይ በመባል ብቻ የሚመጣ አይደለም፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ በመሆንም የሚገኝ ነገር አይደለም፡፡ ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ፍጹም በሆነው ለውጥ እንጂ፡፡ ይሁና ይቅርታን ከነትርጉሙ ማወቅና መተርጎም እንዲቻል ለዛሬው ይቅርታ ምን እንዳይደለ ከሚለው እንጀምርን፡፡
  1. ይቅርታ ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት አይደለም፡፡
    ብዙ ጊዜ በስብከት ተጎትጉተው ወይም የበደለው ሰው ምንም ሳይሰማሙ አስታራቂው አስቀድሞ ስላለቀሰ በይሉኝታ ስሜት እሺ ታርቀናል የሚሉ ሰዎች አሉ፡፡ እኛ በባህሪያችን ከእውነት ይልቅ የስሜቶቻችን ተገዥዎች ነን፡፡ በይሉኝታ ስሜት ተነድተው ይቅርታ ማድረግ አደገኛነቱ ከፍ ያለ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ይቅርታ ከፍፁም መታዘዝ የሚመጣ የውስጥ ውሳኔ ነው፡፡ የሆነ ኃይለኛ ስሜት ወደ እኛ እየጎረፈ መጥቶ ይቅር ወደ ምንልበት መድረክ ጠርጎ እንዲያወጣን መጠበቅ አይኖርብንም፡፡ ግን ጌታ ይቅር ተባባሉ እንዳለው ቃል ሳንጨምርበት ሳንቀንስበት ሌላም መከራከሪያ ሳንሰጥ በልባችን ሪሳይክል ቢን ውስጥ ደብቀን ያስቀመጥነውን የበቀል ስንቅ ከዚያም ውስጥ ቢሆን አውጥተን መጣል ካልተቻለ ዝም ብሎ በማለቀስ ብቻ የምንገልፀው ውጫዊ ገጽታ ይቅርታን አይወክልም፡፡ እግዚአብሔር እኛን እንደተመረጡ ሰዎች ነፃ እንድንሆንለት ይፈልጋል፡፡ በውስጡ ይቅርታን ፍፁም ያላደረገ ሰው ነገር ግን በአንደበቱ ይቅር ብያለሁ ብሎ በልቡ ቂመን ሸፍኖ የሚኖር ሰው መንፈሳዊ ነፃነት ይሰማዋል ማለት አይቻልም፡፡ " እኔ ይቅር እንዳልኳችሁ እናንተ እርስ በእርሳችሁ ይቅር ተባባሉ" ጌታ የእኛን ኃጢአት ሙሉ በሙሉ ይቅር ብሏል እንጂ ወደ ኋላ ያስቀረው የለም፡፡ ስለዚህ ይቅርታን የምንማረው ከጌታ ከራሱ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ ይቅርታን የጊዜው ስሜት ብቻ አድርገን መውሰድ የለብንም፡፡

  1. ይቅርታ ተበዳዩ የሚጠይቀው አይደለም፡፡
    አንዳንድ ሰዎች ሰዎችን ሲያስታርቁ የተበደለውን ወገን ይቅርታ እንዲጠይቅ ይመክራሉ፡፡ እንዲያውም በበዳዩ እግር ላይ ወድቆ ይቅርታ እንዲጠይቅ ይገፋፋሉ፡፡ ለምን ቢባል አንዴም ምን አለበት? ሰላም ይውረድ እንጂ የሚል መልስ ይሰጣሉ፡፡ አሊያም ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሆኖ አባቴ ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ብሏል፡፡ እስጢፋኖስም እንዲህ አድርጓልና የሚል ቅጥስ ለመጥቀስ ይቃጣቸዋል፡፡
እንግዲህ ይህ በጣም ሰውኛ የሆነ ትምህርት ነው፡፡ የተበደለው ይቅርታ ጠያቂ አይደለም፡፡ ቅዱሳት መጽሐፍትም ይህንን አያስተምሩም፡፡ ይልቁንስ የተበደለ ሰው ሁለት አስፈላጊ ነገሮችን ሊያደርግ ይችላል፡፡ አንደኛው ክርስቶስ ይቅር እንዳለ እንዲሁ በራሱ ይቅር ብሎ ማለፍ፣ ሁለተኛው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረው የበደለውን ወንድሙን ሄዶ መውቀስና ከሰማው ወንድሙን ገንዘብ ማድረግ ማቴ 1815-2ዐ፡፡
ጌታችን ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሆኖ ልብሱን ሲከፋፈሉት የነበሩትን ሰዎች ይቅርታ አልጠየቃቸውም፡፡ የሚሰሩትን ኃጢአት እግዚአብሔር እንዳይቆጥርባቸው አምላኩን ተማፀነ እንጂ ፡፡ " አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" ሉቃስ 2334፡፡ እስጢፋኖስም ቢሆን በድንጋይ የሚወግሩትን ሰዎች እባካችሁ ይቅርታ አድርጉልኝ አላለም፡፡ ነገር ግን ስለ እነርሱ ማለደ፡፡ እንዲህም ሲል " ጌታ ሆይ ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው" ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ ሐዋ 78 ፡፡ ኢየሱስ ይቅርታ ጠየቀ ብንል አንድ የበደለው ወይም የሠራው ስህተት አለ ወደሚለው ድምዳሜ እንዳያመራን እንፍራ፡፡ እስጢፋኖስም ቢሆን ስለ ክርስቶስ ትንሳኤ ከመስበክና እውነትን ከማስተማር ውጭ የሠራው በደል ስላልነበረ ይቅርታ የሚጠይቅበት ምንም ምክንያት ስላልታየው ይቅርታን ከሚጠይቅ ይልቅ ስለ በደለኞች መማለድን መረጠ፡፡ ስለ በደሉት ሰዎች ከእግዚአብሔር ይቅርታን መለመንና የበደሉትን ሄዶ ይቅርታ መጠየቅ ሁለቱ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በእርግጥ የተበደለ ሰው ወደ በደለው ወንድም መሄድ ይኖርበታል፡፡ የሚሄደው ግን ይቅርታ እንዲጠይቅ ሳይሆን ሊወቅሰው ነው፡፡ ይህንን ነው መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረን፡፡ የበደለው እያለ የተበደለው ይቅርታ የሚጠይቅ ከሆነ በደለኛው በበደሉ ይቀጥላል፣ ከስህተቱም የሚማርበት ዕድል የለውም ማለት ነው፡፡ የተበደለ ይቅርታ እንዲጠይቅ የሚያሳይ እንዲያውም ኢየሱስ ተበድሎ ይቅርታ እንደጠየቀ ተደርጎ የሚሰጥ ትምህርትና ስብከት አለ፡፡ አንዳንድ ዘማሪዎችም እንዲህ አድርገው ዘምረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ወደ ቃሉ መሠረት መመለስ ጠቃሚ ነገር ነው፡፡ ይቅርታ ማድረግም ይሁን ይቅርታ መጠየቅ እንደ እግዚአብሔር ቃል አስተምህሮት መሆን አለበት እንጂ ይቅርታ መጠየቅ የተበዳይ ኃላፊነት አይደለም፡፡
  1. ይቅርታ ሰው የሠራውን ጥፋት ችላ ማለት አይደለም፡፡
አንዳንድ ሰዎች አጥፊው ከነጥፋቱ ችላ ከተደረገ ሌላ ምን ያስፈልጋል ብለው ስለሚያስቡ ይቅርታ ማድረግን ቸል ይላሉ ወይም ይቅርታ ለማድረግ ያቅማማሉ፡፡ የፈለገውን ይሁን እኔ እርሱ ጋ ካልደረስኩ እርሱም እኔጋ ካልደረሰ ምንም ሳንቸገርና ሳንቀያየም መኖር ስለምንችል እርሱ ያደረገብኝን ለማሰብ አልፈልግም ይላሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ያደረገብኝን ነገር ንቀው ስለ ተውኩት አሁን ምንም አያስፈልገኝም ይላሉ፡፡
እነዚህ ሁሉ መልካም ሐሳቦች ይመስላሉ፡፡ ግን መልካም ሐሳቦች ሳይሆኑ በውስጣቸው ችግር የቋጠሩ ናቸው፡፡ እንዲያውም እውነተኛ ከሆነው የይቅርታ ሕይወት ተስፈንጥረን እንድንወድቅ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ይቅርታ ማድረግ ለተበዳዩም ለበዳዩም ለሁለቱም ጥቅም ነው፡፡ የተበደለውን ሰው ለማጽናናትና የበደለውን ለመኮነን የሚደረግ ይቅርታ የለም፡፡ ለሁለቱም ከሚሰጠው ጥቅም አንፃር ብናየው ጥሩ ነው፡፡
ከይቅርታ አድራጊው አንፃር፡- ይቅርታ አድራጊ የምንለው የተበደለው ሰው ነው፡፡
    • እርሱ በደል ያደረሰበትን ሰው ይቅርታ በሚያደርግበት ጊዜ ራሱን ከመራርነት እስራት ነፃ ያደርጋል፡፡ ምንም እንኳን ንቄ ትቼዋለሁ ቢልም ስለ ሰውዬው ባሰበ ቁጥር መመረሩ አይቀርም፡፡ ይቅርታ ሲያደርግ ግን የውስጡ ምሬት ተወግዶለት እረፍት ያገኛል፡፡
    • ይህ ብቻ ሳይሆን ይቅርታ ካላረገ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቅርታ አያገኝም፡፡ አንዳንድ ሰው እኔ አላዘንኩም ይል ይሆናል፡፡ ቢሆንም ክርስቶስ ይቅር እንዳለ ለሰዎች ይቅር ማለት ካልተቻለ ከእግዚአብሔር ምህረትን አገኛለሁ ማለት እንዳይችል ቃሉ በግልጽ ይነግረናል፡፡ #ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ይቅር ይላችኋልና ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁምና፡፡; ማቴ 614-16
    • የሰዎች ፀሎትና ፆም በእግዚአብሔር ፊት ሊከበር የሚችለው የበደልን እስራት ሲፈቱ/ ይቅር ሲሉ ነው/ ኢሳ 586/. በጣም ብዙ ፀሎት ይደረጋል፡፡ ለአያሌ ቀናት የፆምም ይጨመርበታል፡፡ የፀለይነውንና የፆምነውን ያህል ግን መንፈሳዊ ተሐድሶ የመንፈስ ቅድስም አሰራር አይገለጥም፡፡ ምክንያቱም ፆምና ፀሎት ከበደል እስራት ጋር ነው፡፡ ከቂም ጋር ነው፡፡ ይህ በመሆኑ የብዙዎች ፈውስ ዘግይቷል፡፡ ብዙዎች ተበድለው ሳለ ይቅርታን ማድረግ ባለመቻላቸው በታላቅ ቁዘማ ውስጥ አሉ፡፡
ከይቅርታ ተቀባዩ አንፃር፡-
ይቅርታ ተቀባዩ ወንድሙን የበደለ ሰው ነው፡፡ እርሱ ደግሞ በደሉን አውቆ ይቅርታ መጠየቅ ይኖርበታል፡፡ ይህንን ሲያደርግ ከዕዳ ነፃ ይሆናል፡፡ ወንድሙን የበደለ ሰው ነገ የሚከፍለው ዕዳ አለ፡፡ ዛሬም ቢሆን የህሊና ክስ ውስጥ ይኖራል፡፡ "አትሳቱ እግዚአብሔር አይዘበትበትም፡፡ ሰው የሚዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፡፡" ገላ 67
ወዳጆች ሆይ፡ ራሳችሁን አትበቀሉ ለቁጣ ፈንታ ስጡ እንጂ በቀል የእኔ ነው እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ፡፡ ሮሜ.1219 ይህ ማለት ታዲያ እግዚአብሔር በበደለኛው ሰው ላይ ይፈርድበታል ለተበደለውም በፅድቅ ይበይናል ማለት አይደለምን? የእግዚአብሔርን ቃል መጽሐፍ ቅዱስን ስንመለከት በሰዎች ላይ በደል ያደረሱ ነገር ግን ከሰውም በእግዚአብሔርም ምህረትንና ይቅርታን ያልለመኑ ሁሉም ብድራታቸውን ተቀብለዋል እንጂ ሳይቀጡ አልቀሩም፡፡ በዳዩ በደሉን አውቆ ከወንድሙ ይቅርታ ቢጠይቅ እግዚአብሔርንም ምህረት ቢለምን ሙሉ ነፃነት ያገኛል፡፡ ለእርሱም ጥቅም አለው የምንለው ለዚህ ነው፡፡

  1. ይቅርታ ውስጣችን እየታመመ ለማስመሰለ የምናደርገው ጉዳይ አይደለም፡፡
    ይቅርታ አድርጌአለው እየተባለ ህመሙ ካልዳነ ይቅርታው እውነት አልነበረም ማለት ይቻላል፡፡ አሁንም ደጋግመን በዓመቱ የተደረገብኝ ነገር እየተባለ የሚመረር ከሆነ እውነተኛ ይቅርታ አልተደረገም ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ልብ እያዘነ ምንም አልተቀየምኩም እያሉ አብሮ መብላትና መጠጣት እርስ በእርስ መሳሳም አደገኛ ባህሪይ ነው፡፡ እንደዚያ የሚያደርጉ ሰዎች የበደላቸውን ሰው የሚጥሉትን ገመድ ወይም ወጥመድ የሚፈልጉ ናቸው፡፡ በውስጥ የጋለ ጥላቻ ስሜት ይዘው በውጭ ሰውነታቸው ግን የፍቅር ፊት የሚያሳዩ አደገኛ ክርስቲያኖች ከኢየሱስ መማር አለባቸው ፡፡ ኢየሱስ በተቆጣ ጊዜ በቤተመቅደስ ውስጥ ያለውን ገበታ ገለበጠ እንጂ ስቆ ወይም አሽማጥጦ አላለፈም፡፡ ዮሐ 215-16፡፡ ልቡ ስለሰዎች አለማመን ባዘነ ጊዜ አለቀሰ እንጂ አልሳቀም ዮሐ. 11፡፡ አሁን አማኞች የምናሳየው ባህሪይ ኢየሱስ ካሳየን ምሳሌያዊ ሕይወት ጋር የሚቃረን በመሆኑ መለወጥ አለበት፡፡ ክርስቲያኖች የሚያደርጉት ተገቢ ካልሆኑ ነገሮች አንዳንዶችን ለመጥቀስ በወንድማቸው ላይ ሲያዝኑ " ጌታ ይባርክህ" " ኢየሱስ ጌታ ነው" " እኔ እወድሃለው/እወድሻለው/" ይላሉ፡፡ ያውም ያንኑን እየደጋገሙ ያሰሙታል፡፡ ልብ ብለን ስናየው ግን እንደዚህ የሚሉት በእውነት ከልባቸው አይደለም፡፡ ቅሬታን ለመግለፅ ጌታ ይባርክህ የሚል ዐ.ነገር መጠቀም የሚያስፈልግ አይደለም፡፡ በድለኸኛልና አዝኜብሃለሁ ማለት ይሻላል፡፡ በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ጌታ ነው ማለትም ትክክለኛውን ሐሳብ ለተጣመመ ስሜት መጠቀም ይሆናል፡፡ እወድሃለሁ እያሉ መሸንገልም ግብዝነትን ከማጉላት በቀር ሌላ ጥቅምና ትርፍ ስለማይኖረው ያለምንም ማስመሰል አዝኜብሃለው/አዝኜብሻለው/ ብሎ መውቀስ ትክክለኛ የክርስትያን ተግባር ነው ብዬ አምናለሁ፡፡
  1. ይቅርታ ማድረግ ሰዎችን ከኃላፊነታቸው ነፃ የሚያደርግ አይደለም፡፡
    አንድ በደል በይቅርታ ብቻ ሊረሳ ይችላል፡፡ የተሠራውን በደል ተከትሎ ከሚመጣው ኃላፊነት ለመሸሽ ግን አያስችልም፡፡ ለምሳሌ፡ ሚስቱ ሳታውቅ ከሌላ ጋር ያመነዘረ አንድ ሰው ሚስቱን ግልጽ ይቅርታ ቢጠይቅ እርስዋም ብታደርግለት ነገሩ እዚያ ጋ ሊያበቃ ይችላል፡፡ በእግዚአብሔርም ፊት በሠራው በደል ምህረት ቢለምን ጌታም ይቅር ይለዋል፡፡ በዚህ ወቅት ልጅ ወልዶ ቢሆን ግን ያንን ልጅ የማሳደጉ ኃላፊነት ይጣልበታል እንጂ ባሌቤቱንና እግዚአብሔርን ይቅርታ ስለጠየቀ ከኃላፊነት ነፃ ይሆናል ማለት የሚቻልበት መንገድ የለም፡፡ ባለቤቱም ይቅርታ ስላደረገችለት ተብሎ እንደ ልÍ እንድትቀበለው ማስገደድ አይቻልም፡፡ ከዚህም ባለፈ የምንዝርና ኃጢአት በፈጸመበት ወቅት ምናልባት በሆነ ምክንያት የአካል ጉዳት እንደነዓይን መጥፋት፣የአጥንት መሰበር ወዘተ ደርሶበት ቢሆን ያንኑ የመሸከም ኃላፊነት የባለቤቱ ይሆናል እንጂ ይቅርታ ስለተደረገ ዓይኑ አይተካለትም፡፡ እጁን ተቆርጦ ቢሆን አይቀጠልለትም፡፡ ይህንን የሚመስሉ ሌሎችም የኃላፊነት ዓይነቶች ይኖራሉ ማለት ነው፡፡
  2. ይቅርታ ማድረግ ጀግንነት ወይም ትምክህት አይደለም፡፡
    ማንኛውንም ነገር ብናደርግ ማድረግ የሚገባነንን ግዴታ ተወጥተናል እንጂ ያንን ስለ ሠራን በፊታችን የምናስነፋው ምንም ዓይነት መለከት ሊኖር አይገባም፡፡ እኛ ባለንበት ዘመን አገልጋዮች እንè ሳይቀሩ ይቅርታ ስላደረጉ ትምክህት ይሰማቸዋል፡፡ እግሬ ላይ ስለ ወደቀና ስለተማጠነኝ እንጂ እስከ መቼውም ዓይኑን አላየውም ነበር የሚሉ ብዙ ናቸው፡፡ ነገር ግን ይቅርታ ማድረግ የሚኖርብን በዳዩ ስለተማጠነና እግር ላይ ስለወደቀ ሳይሆን ጌታ ስለታዘዝን ብቻ የሚደረግ መሆን አለበት፡፡ በዳዩ ባይጠይቅና መጥቶ እግር ላይ ባይወድቅ ይቅርታ አናደርግም ማለት ነው? ከፍ ብሎ የተመለከትነው ይህንን ነው፡፡ ወንድምህ ቢበድልህ ውቀሰው ይላል ቃሉ፡፡ በወቀስነው ጊዜ በዳዩ አላውቅልህም ምንም አልበደልኩህም ቢል ሁለት ወይም ሦስት ምስክሮችን ይዘን ሄደን እናነጋግረዋለን፡፡ እነርሱን ባይሰማ ወደ ቤ/ክ ሽማግሌዎች እናቀርበዋለን፡፡ ቤ/ክንን ባይሰማ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁን ይላል ማቴ.1815 -20፡፡ ይህ ማለት ግን የበደለንን ሰው ይቅር አንለውም ቂምን ይዘን እንቀጥላለን ማለት ነው? በእርግጥ እንደዚህ አይደለም፡፡ በዳዩ ይቅርታ ቢጠይቅም ባይጠይቅም፣እግራችን ላይ መጥቶ ቢወድቅም ባይወደወቅም እኛ ስለ ታዘዝን ብቻ የበደለንን ይቅር የማለት ግዴታ አለብን፡፡ ስለዚህ ይቅርታ ያደረገ ሰው እነ እገሌ ስለለመኑኝና እርሱም ስለ ወተወተ ይቅር አልኩት እንጂ ወደብዙ ቦታ አደርሰው ነበር እያለ መፎከር ያለንን የመንፈሳዊ ሕይወት ለፈስፈሳነትን የሚያመላክት ነው፡፡

  1. ይቅርታ አለ ማድረግ የበደለንን ሰው የምንጎዳበት መንገድ አይደለም፡፡
    እውነት እንነጋገር ካልን ይቅር አልልም የሚል ሰው የሚጎዳው ራሱ ነው እንጂ የበደለ ሰው አይደለም፡፡ የበደለን ሰው ይቅርታ የመጠየቅ ግዴታ ያለበት እንደሆነ ሁላችንም እንስማማበታለን፡፡ የሚገርመው ነገር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጎልቶ የሚታየው የበደልናቸውን ሰዎች ይቅርታ እንድንጠይቅ ከሚያዘን ክፍል ይልቅ የበደሉንን ይቅር እንድንል የሚያዘን ትምህርት ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሰዎችን ይቅር ባለማለታችን በጣም አድርገን የምንጎዳቸው ይመስለናል፡፡ እነርሱ ግን አይጎዱም፡፡ ከእግዚአብሔርም ጋር ያጋጨናቸው ወይም ከባድ ወደሆነው የእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ ያስገባናቸው ይመስለንም ይሆናል፡፡ ሚስጥሩ ግን እንደምናስበው ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት በተበዳዩና በበዳዩ መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ አንዱ እግዚአብሔር የሁሉ አባት ነው፡፡ ተበዳዩ በዳዩን ይቅር ባይለው የበደለው ግን ይቅርታ ቢጠይቅና በእግዚአብሔርም ፊት ንስሐ ቢገባ የተበደለው ይቅር አልልም ስላለ ብቻ በደለኛው ታስሮ ይቀራል ማለት አይቻልም፡፡ የአንድ ቀን ስህተት ሕይወትን እንደሚያጠፋ ሁሉ የጥቂት ደቂቃ ንስሐ በእግዚአብሔር ፊት ባለ ብዙ ሞገስ ልታደርግ ትችላለች፡፡ በእርግጥ ነው የሚለው አማኞች ከዚህ አንፀር ራሳችንን ስንፈትሽ ብዙ ጉድለቶች አሉብን፡፡


ማጠቃለያ፤ እንግዲህ ከላይ ያየናቸው ይቅርታን ስለማድረግ አስመልክቶ ያሉን ግን በመጠኑም ቢሆን የሚታዩብን ስህተቶቻችን ናቸው፡፡ ይቅርታን እንደስሜት የሚያዩ ሰዎች ከስሜትነት ወደ እውነተኛ ተግባር መለወጥ ይኖርናቸዋል፡፡ ተበዳዩ ይቅርታን እንዲጠይቅ የሚያበረታቱ፣ የሚያስተምሩ፣ የሚሰብኩና የሚዘምሩ ወገኖችም እንዲህ ዓይነት የመጽ/ቅዱስ ትምህርት ስለማይኖር ሁሉንም እንደቃሉ እውነት ማድረግ ይኖርባቸዋል ባይ ነኝ፡፡ ተበድለንም ቢሆን በደልን ቸል ብሎ ማለፍ እውነተኛ የይቅርታ መንፈስን ስለማይገነባ የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረው ውይ መውቀስ ወይ ከልብ በሆነ ይቅርታ ይቅር ብሎ ቂምንም ከውስጥ በማውጣት እረፍት ሊያገኙ ይገባቸዋል፡፡ እንደግብዞችም የማስመሰል ይቅርታ በፍጹም ማበታታት የለብንም፡፡ በደል በይቅርታ የሚታጠብ ቢሆንም አንዳንዴ ተከትሎት የሚመጡ የተለያዩ የኃላፊነት ዓይነቶች መኖራቸውን መዘንጋት ተላላነት ይሆናል፡፤ ስለዚህ እንደ ክርስትያኖች የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረን ራሳችንን በመፈተሸ ወደ እውነተኛ ይቅርታ መመለስ ይኖርብናል፡፡ ታዲያ እውዊነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይቅርታ የቱ ነው የሚለውን ለመዳሰስ የሚቀጥለውን ክፍል ሁለት ይመልከቱ፡፡

Tuesday, January 21, 2014

ውርጃ የዘመናችን ቤተ ክርስቲያን ተግዳሮትና የትውልድ ማጥፊያ

ውርጃ፣ የዘመናችን ቤተ ክርሰቲያን ተግዳሮትና የትውልድ ማጥፊያ
ከፓስተር ሳሙኤል ሾንጋ
E-mail satemefe@yahoo.com

አርጄንቲናዊው ሪቻርድ ቶሬ እ.. . ምቤር 11 ቀን 2013 ላይ ድል ባለ ድግስና በቃል ኪዳን ሥነ ሥርዓት በወንዝ ዳር ከቆመ ትልቅ ዛፍ ጋር የጋብቻ ሥነ ሥርቱን መፈሙን የሰማና ያየ ሁርሟል፡፡ ቶሬ የጋብቻ ሥነሥርዓቱን ሲፈጽም ብዙ ታዳሚች፣ ሚኒስክርት የለበሱ ሴቶች ሚዜዎችሚዜዎች፣ አበባ በታኝ ልጆች፣ ካሜራ ባለሙያዎችና ሌሎችም ታዳሚዎች ተገኝተዋል፡፡ የሚያምር ነጭ ሙሉ ልብስና አሬንጓዴ ባርኔጣ አድጎ ከወደደው ንጨት ጋር ጋብቻውን የጸመው ቶሬ በአስፈጻሚዎቹ አማካይነት ከፍቅረው ዛፍ ጋር ጋብቻ ቃል ኪዳን ከፈጸመ ኃላ ቀለበትም አድርጓል፡፡ በእድምተኞቹ ፊት ፉን እወድሻማለት አቅፎመና ከላሰ በኃላ የተያዩ የምግ ዓይነቶችንም ጋዟል፡፡ ቶረ የጋብቻ ሥነሥርዓቱ በፈረንጅ አገር ሰው ለሰው ከሚደረገው ሠርጎች የሚበልጥ እጂ የሕዝብ የተገኘበት ነው፡፡ ይህንን ላና ለሰማ እውነተኛ ክርስያን ሁሉ ሰይጣን በረቀቀ መንገድ እየሠራ መሆኑ በደንብ ገባዋል፡፡ እግዚአብሔር ለሰዎች የሰጠው ክቡር ጋብቻ ምን ያህል እየረከሰ እንደሆነ ለመገመት አያስቸግርም፡፡ ከጋብቻ ጋር በተያያዘ የሻሮን ቴንዳሌ ጋብቻ ሌላው አሳዛኝ ክስተት ነው፡፡ 9 ዓመት በፊት ፣የ41ዓመቷ እንግሊዛዊቷ ቱጃር ሻሮን ቴበታህሳስ ወር 2005 ልፊን ጋር ጋብቻን የፈጸመችው የሚያምር ቬሎ አድርጋ የሙሽራውን ጉንጭ ደጋግማ በመሳም ነው፡፡ ከጋብቻዋ በፊት ለ15 ዓመታት ያህል ከዶልፊኑ ጋር የተቀራረበው ቴንዳሌ አንድ ቀን ያልጠበቀችው ነገር ገጠማት፡፡ ከፍቅረኛዋ ከዶልፊን ጋር ለመዋት ከገባችበት ባህር ውስጥ ሳትመለስ በዚያው ፍጸሜዋ ሆነ፡፡
የዚህ አጭር ጽሑፍ ዋና ዓላማ ስለ ጋብቻ ለማሳሰብ ሳይሆን ባለንበት ዘመን የሰው ልጅ በምን ዓይነት ውድቀት ውስጥ እንዳለ ለማሳየትና እንድንነቃ ለማድረግ ነው፡፡እንደነዚህ ዓይነቶች አሳፋሪና አሳየሆኑ፣ የሰው ልጆች ውድቀቶችን መስማት ተራ ነር እየሆነ ጥቷል፡፡ እንደነዚህ ዓነቶች ነገሮች ለቤተክርቲያን ትልቅ ተግዳሮት እንና የተጣለባትን ኃፊነት በእነት በቅንነት፣ በትጋትና ታማኝነትም እንትወጣ የሚያለክ፣ጌታም በደጅ ሆነ እንናስተውል የሚያደር የማቂያ ደወል ናቸው፡፡ የጋብቻ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የዘመናችን ቤተክርስቲያን ሌላ ብዙ ፈተናዎች አሉባት፡፡
21ኛው ክፍለ ዘመን መንግሥታትንና ቤተክርቲያናትን ከሚፈታተኑት ጉዳዮች ሌላውና ዋንኛው ውርጃ ወይም አዲስ ከመጣው አጠራሩ መረት ጽንስ ማረጥ ነው፡ ጽንስ ማረጥ ጋር በተያያዘ ዘርፈ ብዙ የሆኑ ሙግቶች ሲደመጡ ኖረዋል አሁንም እየሰማናቸው እንገኛለን፡፡ ከዚህ አንጻር ቤተክርቲያ ልትጫወት የሚገባ ሚና እጅግ በጣም ከፍመሆኑን ውርጃና ተለዋዋጭ ገጽታው፣ በዘርፉ የሚሰነዘሩ ሙግቶች እና ከፍተኛ ፍጥነት የታከለበት ዕድገቱ ይጠቁማሉ፡፡ ቤተክርስቲያ ከማንም በላይ ቀድማ ለፍትህ መቆም ሕይወትን ለመታደግና ለድምጽ አልባዎች የምትገት መሆን እንዳለባት ከጌታ የተቀበለችው ኃላፊነት ያስገድዳታል፡፡ የምንሰብከው የእግዚአብሔር ቃል መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሕገ መንግሥት ስለሆነ በሙላት ሊሰበክ የሚገባው ሲሆን ለዚህም ቀዳሚ ሚና ጫወት የሚበቅባት እግዚአብሔር በምድር ላይ የራሱ እንደራሴ አድርጎ ያስቀመጣት ቤተክርስቲያን ናት፡፡ ባደጉና ዴሞክራሲያዊ በሆኑ አገሮች የሕናትን መብት መጣስ፣ሕጻናትን ማጥቃት ( Child abuse ) ፣ሕጻናትን ለጦርነት መጠቀም ፣ ከአቅማቸው በላይ ሥራ ማሰራት እና ወዘተ ከፍተኛ ቅጣት የሚያስከትል አደገኛ ወንጀል ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ለዓለም ሁሉ በማስተጋባት ጉልህ ሚና የመጫወት ኃላፊነት የሚጠበቅባት ቤተክርቲያን ከዴሞክራት አገሮች በላይ ለዚህ ጉዳይ ልትቆም ይገባታል፡፡
ባለጋራችን ዲያብሎስ የእግዚአብሔር ዓላማ በሰዎች ሕይወት እንዳይከናወን ከሚያደርጋቸው ስልቶች አንዱ ሊወለዱ ያሉ ሕጻናትን ማስጨንገፍ ወይም ከተወለዱም በኃላ በጅምላ እንዲጨፈጨፉ ማድረግ ነው፡፡ የእሥራኤል ልጆች በምድረ ግብጽ እየበረከቱ ሲሄዱ ያየ ንጉሥ ይህንን ሕዝባዊ ዕድገታቸውን ለመግታት ያደረገው ሙከራ የዕብራውያን ሕጻናት ሳይወለዱ በሆድ ውስጥ እንዲጨነግፉ ማድረግ እንደነበር ኦሪት ዘጸት ምዕራፍ አንድ ላይ የምናገኘው ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ ንጉሥ ሆኖ መወለዱን በመስማቱ የደነገጠው ንጉሥ ሄሮዲስ በቤተልሔም አራጃ ያሉ ዕድሜአቸው ከሁለት ዓመት በታች የሆናቸው ሕጻናትን እንዳስጨፈጨፋቸው ወንጌላዊው ማቴዎስ በስፋት ተርኮልናል( ማቴዎስ ወንጌል 2)፡፡ የሔሮዲስ ሰይፍ ሰዎችን ለማዳን ሲል በእግዚአብሔር እቅድና ፈቃድ የተወለደውን ጌታና የዘመናት ንጉሥ የሆነውን ኢየሱስን ማግኘት ባይችልም ብዙ ሕጻናትን ሕይወት ቀጥፏል፡፡
በዘመናችንም ደግሞ ሰይጣን መልኩንና አሠራሩን ቀይሮ በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጠፋቸው ልጆች ቁጥር አስደንጋጭ ነው፡፡ በክርቲያናዊ ትምህርትና በሥነ መለኮት በተለይም በስይስተማቲክ ቲዮሎጂ ቁልፍ ሰው የሆኑት ዶር ኢዩኤል አር ቢኪ ታላላቅ የዓለም ጦርነቶች ከጨረሱአቸው ሰዎች ይልቅ በውጃ ምክንያት የሚያልቁ ሕጻናት ቁር በእጥፍ ንደሚበልጥ ያትታሉ፡፡ እንደ ቢኪ ባባል እንደ አውሮፓውያን ቆጣር በ2005 ሆስፒታሎችና የጤና ጣቢዎች በሜሪካን 1.2 ሚሊዮን ውርጃ ሲያከናው በካናዳ ደግሞ ከ96 ሺህ በአከናውነዋል፡፡ በአሜሪካን ከ1973 .. ጀምሮ በካናዳ ደግሞ ከ1969 .ም ጀምሮ ከ53 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ሕጋዊ ውርጃ ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በሁለቱም አገሮች ያለው የሕዝብ ብዛት 350 ሚሊዮን ሲሆን ካለው የሜሪ ሕዝብ ብዛት ጋር ሲነጻሕጋ ውርጃ የሚያቀው ቁጥር ከአጠቃላይ የሕዝቡ ቁጥር አንድ ሰባተኛ ጋር እኩል ነው፡፡ ይህም የሚሆነው እንግዲህ የሕጸናት መብት ቀዳሚ አጀንዳ በሆነባቸው ፣ የሰለጠኑና ዴሞክራት በሆኑ አሜሪካንና ካናዳን በሚመስሉ አገሮች ነው፡፡የታሪክ ምሁራንም እንደሚገምቱት የናዚ ጀርመን ጅምላ ጭፍጨፋ 6ሚሊዮን አይሁዶችን ጨምሮ ከ10-11 ሚሊዮን ነጻ ሰዎችን ፈጅቷል፡፡ ከእነዚያ መካከል አብዛዎቹ ሕጻናት ናቸው፡፡ የሚያሳዝነው ግን በውርጃ ምክንያት የሚሞቱ ሕጻናት ቁጥር ከዚህ ሁሉ በብዙ እጥፍ እየበለጠ መሆኑ ነው፡፡1
እንደ አሜሪካ ባሉ ሰለጠኑ አገሮች የጽንስን ሕይወት ማጥፋት ይም ጽንስ እንዲረጥ ማድግ እንደ ወንጀልም እንደ ነውርም አለመቆጠር ብቻ ሳይሆን እንደ ብት እየታሰበ ሲሆን ይህንን የሚያጎለብቱ ብዙ ሙግቶችና ጠንካራ ክርሮች እየተደመጡ መሆናቸው የጉዳዩ ተፋላሚዎች ከሆኑት ይልቅ የደጋፊዎችን መጠን እያሳደገ መጥቶአል፡፡ የምዕራባውሥርዓተ አልበኝነትን ኑሮ እንደ ሥልጣኔ የቆጠሩ አንዳንድ 3ኛው ዓለም ሕዝቦችም ይህንኑን መንገድ መከተላቸው ደግሞ በጣም አስገራሚም አሳሳቢም ነገር ነው፡፡ የምዕራቡም ሆነ ሌላው ሕዝብ በእንዲህ ዓይነት መሥመር በሳተ የልምምድ ማጥ ውስጥ እንዲዘፈቅ ያደረገው በየጊዜው የሚደመጠውና በውስጡ ክፋት የቋጠረው የምሁራንና የፈላስፋዎች አሳብ በተራው ሕዝብ አእምሮው ውስጥ ዝግ ባለ አኳኃን እየሰረጸ መምጣቱ ይሆናል ብሎ መገመት ይቻላል፡፡ ግዚአብሔር ቤት ቅናት ያላቸው ምሁራንና ፈላስፋዎች ንዳሉን ሁሉ መርዘኛ አስተሳብ የተሞሉም እዳሉ አካድምና፡፡
እንግዲህ ካታ ምሁራንና አጢኚዎች ባደጉት ዳሰሳ ውጃን ከግብረ ገባዊና ከህጋዊ አቅዎች /Moral and Legal aspects/ አንጻር ለመተንተን ሞረዋል፡፡ በትንተናቸውም በመንተራስ ለሚከተሉት ጥያቄዎች መልስ ለመጠት ጥረዋል፡፡ ውርጃ የሕግ ተገቢነት ያለው ነውን?፣ ጽንሱ ንዳች ሕጋዊ ወይም ምግባራዊ መብት አለው ወይ?ጽንሱ ወይም ሽሉ ሰው ነው ተብሎ ከለላ ሊደረግት ይገባዋል ወይ? ሰው የመሆንስ መስፈርቱ ምንድነው? እና ርግዝናው በሥወት ሂደት ከሴት የንቁል ዘር ጀምሮ እስከ መወለድ ድ/ from Unicellular zygote to birth/የሚያሳየውን ጉልምስና እንዲረጥ የሚያስችል ንዳች ግብረ ገባዊ አግባነት አለ ወይ? የሚሉና ወዘተ ናቸው ፡፡ የብዙ ምሁራን ጥናታዊ ዳሰሳ ቀጥሎ ያሉ አስተቦችን በመተንተን የጥያቄዎችን መልስ እንድናገኝ በጥቂቱ ግዘናል፡፡
1 ውርጃ በሚመለከት ሦስት አመለካቶች
1.1 ፅንፈኛ ወግ አጥባቂ አመለካካት(Extreme conservative view) ይህንን አስተብ የሚያራምዱት ሙሉ በሙሉ የውጃ ተቃዋሚዎች ሆኑ የካቶክ ቤተክርስቲያን ግንባር ቀደም ናት፡፡ የዚህ አስተሳሰብ አራማጆች በያዙት ጠንካራ አቋም መሠረት ከሆነ ሰው ማለት በሴት ሆድ ከእቁላል ዘር ፈጠር ጊዜ ጀምሮ ያለው ማንነቱ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን አንድ ፅንስ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል የተፈጠረ ሰው ስለሆነ (by virtue of Imago- Die) ውርጃ ሊደረግበት አይገባም ብለው ያምናሉ፡፡ የዚህ ትልቁ ጥቅም ወይም ብልጫው የሰውን ሰውነት ከሴት የእንቁላል ዘር ጀምሮ ያለ እንደሆነ አድርጎ ፊቺ የሚሰጥ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ ውርጃን በፈጸም ሰውን መግደል ወይም ነፍስ ማጥፋት ነው፡፡
1.2 ጽንፈኛ ለዘበብተኘኛ አመለከካከተት(Extreme liberal view) የዚህ አመለካራማጆች ውጃን የሚደግፉ ናቸው፡፡ በእነርሱ አገላለጽ መሠረት ሰው ሰውነት የሚጀምረው ከማህፀን ከወጣ በኃላ ከዚያ ቂት ቆይቶ ነው፡፡ ስለህ ሰው ለማት ተገወቅት የውልደት ጊዜ ወይም ከዚያ በኃላ ለው አጭር ጊዜ ምናልባት እስከ አንድ ወር ድረስ ያለው ጊዜ ሲሆን ውርጃ ተገቢ መሆ አለመሆን የሚወስነው ከዚህ ንጻር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አመለካከት ችግር የተሸከመ ነው፡፡ ለምሳሌ ከመወለዱ 5 ደቂቃ በፊት በማህፀን ውስጥ ባለ ሕጻንና ከማሕጸን ከወጣ አንድ ደቂቃ በሆነው ሕጻን መካከል ያለው ልዩነት ምን እንደሆነ በግልጽ ሊያስቀምጥ የሚችል አለመሆኑ ነው፡፡
1.3 መካከለኛ አመለካከት(Moderate view) ህ ከመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ይልቅ ለስላሳ የሆ አመለካከት ነው፡፡ በእህ አመለካከት መሠረት ጽንስ መ ያለበት ተገቢ ጊዜ በሥ ሕይወታዊ ዕድገት ሂደት ወቅት ነው፡፡ ይህ ጊዜ ደግሞ ከሴት እንቁላል ዘር ጀምሮ እስከ መወለድ ባለው ጊዜ ነው፡፡ ዚህ አሳብማጆች ጽንሱ ከእርግዝና ወደ ልጅነት ዝግ ባለ ሂደት ውስጥ የሚያልፍ ንድ ቁም ነገር ላይ ያለ ዘር ነው ሰው አይደለም ብለው ይሞግቱናል፡፡ እንግዲህ ይህ ማለት ከእርግዝና እስከ ልጅነት የተለያ የሰውነት(ብአዊነት) ደረጃዎች ይኖራሉ ማት ነው፡፡
ከላይ ከተመለከትናቸው በተጨማሪ ሌሎች የምናያቸው ሙግቶች ደግሞ አሉ፡: Internet Encyclopedia of Philosophy ሙግቶቹን በይከፍላቸዋል፡፡ መጀመሪያው ዋና ሥነ ሥርዓት ክርክር(Standard Argument ) ሲሆን ሁለተኛው ገላጭ የሥነ ሥርዓት ክርክር(Modifier Standard Argument) ይባል፡፡
ዋና የሥነ ርዓት ክርክር ሎገሲም Syllogism የተባለ ዝርዝር ትንበማቅረብ ውርጃን ይቃወማል፡፡
የሰውን ልጅ መግደል ክልክል ነው፡፡
ሽል የሰው ልጅ ነው፡፡
ሽልን መግደል ክልክል ነው፡፡
የሰውን ሕወት መግደል የተከለከለ ስለሆነ ሽልን መግደል በፍጹም የተከለከለ ነው የሚል አም ይዘዋል፡፡ ይህ አም ሙሉ በሙሉ ጽንፈኛ ወግ አጥባቂ ከሆነው አመለካት ጋር የሚዛመድ ነው፡፡ ኖርበርት ሆርስተር የተባሉ ውቅ የጀርመን ፈላስፋ "ሽል እንደ ማንኛውም ማለትም ደ ሌሎች ሁሉ ሙሉ ሰው ስሆነ ሽልን መግደል የተከለከለ ነው" ብለው ይከራራሉ፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ሆርስተን የአእምሮ ህመምተኞችና የአካ ጉዳተኞችም እንደ ማንኛችንም ሰዎች ስለ ሆኑ ልዩ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ያሳስባሉ፡፡
ገላጭ ወይም አሻሻይ ዋና ሥነ ሥርዓት ክርክር የመጀመሪያው የሆነውን የዋና ሥነ ሥርዓት ክርክርን አሳብ በራሱ መንገድ በማሻሻል ወሰብሰብ ያለ መከራከሪያውን ያቀርባል፡፡ ሽልን በተመለከተ የሰው ልጅ Human ሚለው ቃል ፋንታ የሰው ሕይወት ዓይነት Human life formሚለውን ተክቶ ስለሚሟገት ክርክሩ የበለጠ ውስብስብ ሆነ፡፡ ይህንን አመለካከት የሚያራምዱ አካላት የሚያቀርቡት ዝርዝር ትንተና( syllogism ) እንደሚከተለው ነው፡፡
የሰውን ሕይወት ዓይነት መደል የተከለከለ ነው፡፡
ሽል የሰው ሕይት ዓይነት ነው፡፡
ሽልን መግደል ክልክል ነው፡፡
የሁለተኛው ክርክር አሳብ ውርጃን ለሚደግፉ ሁሉ ከመጀመሪያው ይልቅ የሚመች ነው፡፡ ምክንያቱም ሽል የሰውን ሕይወት የሚመስል እንጂ የሰው ልጅ አይደለምና ከለላና ጥበቃ ይደረግለት ለማለት የሚያስችል ምንም መሠረት የለንም ወደ ሚለው ድምዳሜ ያደርሳቸዋል፡፡ የዚህ ክርክር አራማጆች እንደ ያዙት አቋም ከሆነ ሰው ሰው የሚሆነው በሂደት እንጂ ከጽንስ ወቅት ጀምሮ አይደለም፡፡
ሌሎች ደግሞ ማለትም እንደነ ጃኔ እንግልሽ እና ማሪ አን የመሳሰሉት በክርክራቸው ወቅት ሰው የመሆን መስፈርት ናቸው ብለው የሚያቀርቡአቸው አሉ፡፡ መስፈርቶቹን በአምስት ምድብ የከፈሉአቸው ሲሆን እንደሚከተለው ያቀርቡአቸዋል፡ እነርሱም 1/ ስነ ሕይወታዊ የመስፈርት ምድብ ነው(Biological sector)፡፡ በዚህ መሥፈርት መሠረት አንድ ሰው ሰው ለመባል ሙሉ እጅና እግር ሊኖረው የሚገባ ሲሆን ይህም መብላትን ፣ መጠጣትንና መተኛትን ያካትታል፡፡ 2/ ሥነ ልቦናዊ የመሥፈርት ምድብ ( psychological sector) በዚህ ምድብ ውስጥ የሚጠበቀው ነገር ቢኖር የጠለቀ አስተሳሰብ፣ስሜት፣ ፍላጎት ፣ ምኞት፣ ከሌላው ጋር የመገናኘት ችሎታው Ability of communication)፣ መሣሪያን መጠቀም መቻል፣ራስን ማወቅን ሁሉ የሚያካትት ነው፡፡ በተጨማሪም በዚህ መሥፈርት ውስጥ መታወቅ ያለበት ደግሞ ሰው ሕመም ና ሥቃይ ሊሰማው ይችል እንደሆነም ጭምር ነው፡፡ 3/ ምክንያታዊ መሥፈርት ምድብ ነው ( Rational Sector)፡፡ ምክንያትን ማቅረብና ጠቅለል ያለ አሳብ መስጠት፣ማቀድና ከልምድ መማርን የሚያካትት ነው፡፡ 4 / ማህበራዊ ምድብ / social sector)፡ በማህበራዊ ምድብ ውስጥ የሚጠበቀው የአንድ ውስን ቡድንና የሌሎች ሕዝቦች አባል መሆንና እንዲሁ ሀዘንንና ፍቅርን መጋራት ናቸው፡፡ 5/ ሕጋዊ ምድብ /Legal sector/ ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚደረስ፣ውል የመፈጸም ችሎታ ና የአንድ አገር ዜጋ መሆን መቻልን ያካትታል፡፡2
እንግዲህ ከላይ የተዘረዘሩ አሳቦች ሰዎች የምናደርጋቸው ቢሆኑም ሰውን ሰው የሚያደርጉ ናቸው ብሎ ማመን ተገቢ የመሆኑ ጉዳይ በጣም አጠያያቂ ሆኖ ሰነበተ፡፡ ሰው እነዚህን አምስት ምድቦችን እሺ ብሎ ባይቀበልስ ሰው አይሆንም ወይ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ሲሉ ሜሪ ዋሬን የተባሉ ሰው እንዲህ ብለዋል፡፡ አንድ ሰው ሰው ነኝ የሚለውን ጥያቄ በሚያነሳበት ወቅት ቢያንስ የሚከተሉትን ሁኔታዎችን ማላት አለበት፡፡ እነርሱም ንቁ መሆንንና ሕመምን የመስማት ብቃት፣ራስን የማነሳሳት እንቅስቃሴ፣እና የራስ ንድፈ አሳብ ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ከማህፀን የወጡ ወይንም የተወለዱ ልጆች ወይም ሰዎች ሊያከናውኑት የሚችሉት ናቸው፡፡ ስለ ውርጃ በምንነጋገርበት ወቅት መታሰብ የሚገባው በሆድ ውስጥ ስላሉት እንጂ ስለ ተወለዱት አይደለም፡፡ ምክንያቱም የተወለዱትን ወይም ከማህፀን የወጡትን መግደል ውርጃ ሊባል ስለማይችል ነው፡፡ ያም ሆኖ አንድ ሽል ከተጸነሰ እስከ ስድስት ሳምንታት ውስጥ የአእምሮው እንቅስቃሴ እንደሚጀምር፣ ስቃይን መለየት እንደሚችል፣ድምጽ እንደሚሰማና ይህም ደግሞ በጥናት የተረጋገጠ መሆኑን ብዙዎች ያምኑበታል፡፡
ጠቅለል ስናደርገው፣ ውርጃን የሚቃወሙና የሚደግፉ የየራሳቸውን ጎራ አበጅተው የየበኩላቸውን ሙግት እየተሟገቱና የየግላቸውን መከራከሪያ እያቀረቡ መሆኑን እያየን እንገኛለን፡፡ እንደ እግዚአብሔር ሰዎች በጉዳዩ ላይ የራሳችንን አሳብ መስጠትነና የአማኞችስ እምነት ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ? የሚለውንም ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል፡፡ ወደዚያ ከመሄዳችን በፊት ውርጃ የተፈቀደ ነው የሚሉ ወገኖች የሚያቀርቡአቸውን መከራከሪያዎች በመገምገም ወደ ምንፈልገው አቅጣጫ እናምራ፡፡ ውርጃ ሕጋዊ ይሁን ፣ጽንስ ማቋረጥ ኃጢአት የለበትም የሚሉ የሚከተሉትን ውስን (specific ) ነጥቦችን መሠረት በማድረግ ይከራከራሉ፡፡ እስቲ እኛም ደግሞ እንገምግማቸው፡፡
  1. ሽሉ የሰው ሕይወት ( ነፍስ ) ስላይደለ መገደል/ መወረድ/ ይችላል፡፡
    በዚህ አባባል መሠረት ሽል በሂደት ሰው ወደ መሆን ደረጃ የሚደርስ እንጂ አሁን በሆድ ውስጥ እያለ ግን ሰው ወይም የሰው ነፍስ አይደለም፡፡ በዚህ ጉዳይ ዋንኛ ተሟጋች የሆኑት ጆይስ አርቶር ሲሆኑ በእሳቸው አቋም መሠረት ሽል በሰው ውስጥ ያለ የአካል ቁራጭ (ቲሹ) እንጂ የሰው ነፍስ ወደምንልበት ማንነት አልደረሰም ፡፡ ይሁን እንጂ እንደዚህ ዓይነቱ ክርክር በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን አስተማሪዎች ዘንድ ተቀባይነትን አላገኘም፡፡ ለምሳሌ ሽልን የሚገልጹ Embryo እና Fetus የ ሚባሉ ቃላት ከግሪክና ከላቲን ቋንቋ የመጡ ሲሆን ትርጉሜውም ለጋ ( Young one ) ማለት ነው፡፡ ሳይንትስቶች ሽልን Embryo ወይም Fetus ሲሉ ስለ አንድ ሌላ ፍጥረት ለመናገር ፈልገው ሳይሆን የጽንሱን አጀማመርና ያለበትን የእድገት ደረጃ እንዲሁም የሚገኝበትን ሁኔታ ለማመልከት ነው፡፡ ለምሳሌ ሕጻን፣ ልጅ፣ አዳጊ ልጅ፣ ወጣት ፣ ጎረምሳ ፣ ጎልማሳ፣ አዋቂና አዛውንት እንደምንላቸው ሲሆን ሽሉም ቢሆን በአካላዊ ዕድገቱ ገና በጅማሬ ላይ ያለ ከመሆን በቀር እንደ ሌሎቹ ሰው እንዳይባል የሚያደርግ መሠረት የለም፡፡3 ጎልማሳውን ሰው በምንልበት መንፈስና አገላለጽ ሕጻኑንም ልጅ ሰው እንለዋለን፡፡ በሁለቱ መካከል የአካልና የእድሜ ልዩነት እንጂ የስብዕና ልዩነት የለም፡፡ እንደዚሁም ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ከተረገዘበት /ከተፈጠረበት/ ጊዜ ጀምሮ ያለ አንድ ሽል ከተወለዱት ልጆች የሚለየው በአካል ቅርጹና በእድሜው ብቻ ነው፡፡የሰው ሰውነት የሚወሰነው በአካላዊ እድገቱ መሠረት ከሆነ ህጻን ልጅን ከጎልማሳ ጋር እኩል ሰው ለማለት አቅም ሊያንሰን ነው ማለት ነው፡፡
    ሽል ማለት በሆድ ውስጥ ያለ ግልገል ወይም ጨቅላ የሆነ ሰው ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን አንድ ሕጻን ከእርግዝናው ጀምሮ የራሱ የሆነ የዘመናዊ ሰው homo sapiens አካል ክፍል ያለው የሰው ዘር እንደ ሆነ በግልጽ የሚያሳይ የሥነ ባሕሪይ መለያ(generic code) አለው፡፡ የሕጻኑ ዲ.ኤን.. ከእናቱ የተለየ መለያ ( distinct code) ያለው ሲሆን ከእናቱ የተለየና በውስጧ በጊዜያዊነት የሚኖር ሰው መሆኑን ያመለክታል፡፡4 በሦስተኛም ደረጃ ዘመናዊ የሕክምና ዜዴ ሽሉ የሰውን ቅርጽ ይዞ እያደገ መሆኑን ያረጋግጥልናል፡፡ ለዚህም አልትራ ሳውንድ የተሰኘው መሣሪያ ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡ ሽሉ በጣም ቀጫጫ ልጅ ቢሆንም የሆነ ጓል ወይም ጠብ ብሎ የተቀመጠ ፈሳሽ ነገር ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ የተወሳሰበና የረቀቀ ማንነት ያለው የሰው ልጅ ነው፡፡ የጥናት መረጀዎች እንደሚያመለክቱ ሽሉ ከተጸነሰ በ3 ሳምንታት ውስጥ የልብ ምቱ በመጀመር ወደ ሌሎች የሰውነት አካላቱ ደም መሠራጨት ይችላል፡፡ በ6 ሳምንታት ውስጥ የአእምሮው እንቅስቃሴ የሚጀምር ሲሆን እጁ፣እግሩ፣ክንዱ፣ቅልጥሙ በሚገባ ማደጋቸውን ከማሳየታቸውም በላይ የእግሮቹና የእጆቹ ጣቶች መሥራት የሚጀምሩት በተረገዘ በ8ኛ ሳምንት ውስጥ ነው፡፡ በመጀመሪያው የ3 ወር ጊዜ ውስጥ ሕጻኑ በሆድ ውስጥ መራገጥና መዝለል ፣ እጆቹን መጨበጥና መዘርጋት ይጀምራል፡፡ ሕጸኑ የሚያሳየው ይህን የሚመስል እንቅስቃሴ እነ ሜሪ ዋሬንነና ጃነኔ እንግሊሽ ሰው የመሆን መስፈርቶች ብለው ከሚያቀርቡአቸ በላይ አልፎ የሚታይ ነው፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሔር አሠራርና አመራረር ላይ ካላመጽን በቀር በምንም መለኪያ ቢሆን ጽንስ ማቋረጥ የነፍሰ ግደያ ነው፡፡
  2. ሽሉ ሙሉ ሰው ሳይሆን የሌላ ጥገኛ ( dependent) ስለሆነ ውርጃን የሚከለክል አግባብ የለም፡፡
    ጆሲ አርቶር የተባሉ ተሟጋች ይህንን በጣም ለማመን በሚያስቸግር አገላለፅ እንዲህ በማለት ያቀርቡታል፡፡ ሸሉ በአንድ ሰው አካል ውስጥ ጥገኛ ሆኖ የሚኖር ቲሹ እንጂ የሰው ነፍስ የለውም፣ በጭንቅላታችን ላይ ያለ ፎፎር ቢፋቅና ብናየው በሰውነት ክፍላችን ላይ ተጠግቶ የሚኖር ቲሹ ነው እንጂ ነፍስ ያለው አይደለም፣ የሽሉም ሁኔታ ከዚህ የተለየ አይሆንም ይላሉ፡፡ የሥነ መለኮቱ ሰው ኢዩኤል ቢኪ ይህን አስተሳሰብ አጠንክረው ተፈታትነውታል፡፡ በእናትዮዋ የሆድ ከረጢት የምትኖረዋ የካንጋሮ ልጅ ካንጋሮ አይደለችም ማለት ነው? ይላሉ ዶር ቢኪ አርቶርን በመገዳደር፡፡ የሚኖሩበት ቦታና ሁኔታ ሽሉን ሰው ከመሆን አያግደውም የሚሉት ቢኪ የጆሲ አርቶር አሳብ በአደገኛ መሠረት ላይ የቆመ ነው ይላሉ፡፡ በእርግጥም የጆሲ አሳብ እግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን ሰብአዊ አእምሮ ያለውንም ሰው ጭምር የሚያስቆጣና የሰውን አፈጣጠር የሚያቃልል አደገኛ አቀራረብ ነው፡፡ ሽል ከጥገኝነት ያለፈ ሌላ ማንነት ስሌለለለው በእናት ሆድ ውስጥ እያለ ሊገደል ወይም ህልውናው እንዲቋረጥ ማድረግ ይቻላል የሚል እምነት ያለው በመሆኑ እጅግ በጣም ክፉና ሰይጣናዊ አሳብ ነው፡፡ ጆሲ አርቶር የሚያቀርቡት አሳብ የሚመቻቸው በርካታ ሰዎች እንደሚኖሩ ጥርጥር የለኝም፡፡ ሽል የሌላ ሰው ጥገኛ መሆን ሰው የመሆን መብቱን ያሳጣዋል ብለን የምንደመድም ከሆነ አንድ ነገር እናስብ ዘንድ ይገባል፡፡ ሁለት ሴቶች ነፍሰ ጡር ናቸው እንበል፡፡ የአንደኛዋ ልጅ እድገቱን ሳይጨርስ ያለ ጊዜው ተወለደና ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ሙቀት ሊሰጥ በሚችል የህክምና መሣሪያ እየታገዘ ሕይወቱ እንዲቀጥል በሙቀት ክፍል ሲቀመጥ፣ የሌላይኛይቱ ልጅ ደግሞ ዘጠኝ ወሩን ቢያጠናቅቅም ገና አልተወለደም ወይም በእናቱ ማሕፀን ውስጥ ይገኛል እንበል፡፡ አንደኛው ልጅ ተወልዶአል ግን ያለ ጊዜው የተወለደ ስለሆነ በሰው ሠራሽ መሣሪያ ጥገኝነት ሥር ነው ያለው፡፡ አንደኛው ደግሞ ጊዜው ደርሶአል ግን ሳይወለድ በእናቱ ሆድ ውስጥ ያለ እድገቱን ያጠናቀቀ ልጅ ነው፡፡ የአርቶር አሳብ የትኛን ነው ሰው የሚለው​? ዕድገቱን ሳይጨርስ ተወልዶ በኢንኩበተር ውስጥ ያለውን ወይስ በእናቱ ማሕፀን ያለውን፡ እድገቱን ሳይጨርስ የተወለደውን፣ የመሣሪያ ጥገኘኛ የሆነውን መግደል ይቻለል ይሉ ይሁንን? አንዲት እናት እንዲህ ዓይነቱን ልጅ ብትገድልስ በህግ ይፈቀድላት ይሆንን? የእግዚአብሔርስ ሕግ እንዲህ ያለውን ይፈቀድ ይሆንን? ዘጠኝ ወራቱ ቢጠናቀቁም ሳይወለድ በእናቱ ማህጸን ያለው ልጅስ እንዲገደል የሚያደርግ የህግና የምግባር አግባብነት የቱ ነው? ልጁ ያለ ጊዜው የተወለደባት እናት ልጅዋን ለመግደል ጩቤ ይዛ ወደተኛበት ክፍል ብትገባስ ሐኪሞቹ ይፈቅዱላት ይሆን? በሙቀት ክፍል ያለውን ልጅ መግደል ሕገ- ወጥ ከተባለ በእናተቱ ሆድ ውስጥ ያለውን ጤናማ ልጅ መግደል እንዴት ይፈቀዳል? በትክክኛና በጤናማ ዓይን ካየነው ሁለቱም ጥገኖች ናቸው፣ ሁለቱም ልጆች ናቸው፡፡ ስለዚህ ለሁለቱም ሕጋዊና መንፈሳዊ ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል::
  3. ሴት በሰውነትዋ ላይ የፈለገችውን የማድረግ መብት አላት፡፡
    እንዲህ ዓይነቱ ደግሞ ሽሉን የተሸከመችው ሴት ስሆት ብትፈልግ መውለድ ፣ባትፈልግ ደግሞ የማስወረድ ሙሉ መብት የእሷ ነው የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ እስከ አሁን የምናወራው እኮ ይህንን ነው፡፡ ፅንስ እንዲቋረጥ የምታደርገው ሴቷ ናት፡፡ በእግዚአብሔር ሕግም በውርጃ ምክንያት የመጀመሪያ ተጠያቂ እናት ናት፡፡ ያገባች ልትሆን ትችላለች ያላገባች ፣ ማን ትሁን ማን እናት ናትና ቀዳሚ ተጠያቂ ናት፡፡ ሴት በሰውነቷ ላይ ሥልጣን አላት፡፡ ይሁን እንጂ ማንም በሰውነቱ ላይ ያለው ሥልጣን ግዱብ ነው፡፡ በሰውነታችን ላይ ሥልጣን ቢኖረንም ሰውነታችንን እንደፈለግነው መጉዳትና እስከ ሞት የሚያደርስ ነገር ልናደርግበት አይፈቀድልንም፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው ራሱን ሊያጠፋ ሲያቅድ ብናየው ይቅርና ጥርጣሬ ቢያድርብን በሰውነቱ ላይ ሥልጣን አለው ብለን ልንተወው አንችልም፡፡ ሕግም አይፈቀድለትም፡፡ አትግደል የሚለው የአምላክ ቃል ሰው የራስንም ሕይወት እንዳያጠፋ የሚያስጠነቅቅ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በማያያዝ ሴት በሰውነትዋ ላይ ሥልጣን አላት ማለት ሽሉ የእናቱ ከሆነው የሰውነት አካል ክፍል አንዱ ነው ወደሚለው አሳብ የሚያመራ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሽሉ የትኛው የእናቱ አካል ክፍል ነው? ያልለተወለደው ሕፃን የልብ ምቱ የማን ነው? የእናቱ? የሽሉ የአእምሮው እንቅስቃሴ ብናይ ያ አእምሮ የማን ነው? የእናቱ? ሌላም ጥያቄ እንጠይቅ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ማሪያም ወደ ኤልሳቤጥ በሄደችበት ወቅት በኤልሳበጥ ማሕፀን ያለው ፅንስ በደስታ እንደዘለለ በሉቃስ ወንጌል 144-45ላይ እናገኛለን፡፡ እዚህ ጋ በሕጻኑ /በሽሉ/ የታዩ ሁለት ነገሮች አሉ፡፡ አንደኛው ደስታ/ሐሴት / ሲሆን ሁለተኛው ዝላይ / ፍንደቃ/ ነው፡፡ ደስታውን የተደሰተው ማን ነው? የዘለለውስ ማን ነው? የስድስት ወር የሆነው ሽል እንጂ ኤልሳቤጥ ራስዋ አልነበረችም፡፡ እርስዋ ልጁ መደሰቱንና መፈንደቁን አረጋገጠችና ለማሪያም ነገረች እንጂ ደስታው የልጁ ነው፡፡ ኤልሳቤጥም ተደስታለች ግን የሽሉ ደስታና ፍንደቃ ከእርስዋ ደስታ የተለየ ነው፡፡ ታዲያ ጽንስ ማቋረጥ ነፍሰ ግድያ አይደለም ማለት እንችላለንን? እንግዲህ ማንኛዋም ነፍሰ-ጡር ሴት ሁለት ሰዎችን ታመለክተናለች፣ያውም ራሷንና ሽሉን፣ምክንያቱም ሽሉ ሰው ነውና፡፡
    ስለ ሰው መብት በምንነጋገርበት ወቅት ስለ አቅመ -ደካሞቹና ስለ ድምጸ- አልባዎቹም ጭምር መሆን እንዳለበት አንዘንጋ፡፡ እናት ልጅዋን የመከላከል፣ ከሞትም የመጠበቅ ኃላፊነት አለባት ፣እኛም ለአቅመ -ደካሞችና ለድምጸ- አልባዎች ዘብ የመቆምና እነርሱን የመከላከል ኃላፊነትና ተጠያቂነት እንዳለብን አንዘንጋ፡፡ እናት ስለ ወለደቻቸው ብቻ በልጆችዋ ላይ የፈለገችውን ማንኛውንም ነገር የማድረግ መብት አላት ማለት ይቻላልን? ይልቁንም እናት ለልጆችዋ መስዋዕትነት የመክፈልና የመታደግ አደራ አለባት፡፡ ከዚህ ጋር አያይዘው፣ ተራክቦና ተዋልዶ የግል ጉዳዮች ስለ ሆኑ ሌሎች ጣልቃ መግባት የለባቸውም የሚል መከራከሪያ የሚያቀርቡ አሉ፡፡ ይህ አባባል እውነትነት ያለው ነው፡፡ ሩካቤ ሥጋ በባልና በሚስት መካከል የሚደረግ የግል ሚስጢር መሆኑን ሁላችንም እናምናለን፡፡ በሩካቤ ስጋ ሁለት ተጋቢዎች ጥልቅ የሆነ የቅርብ ግንኙነትና ትውውቅን( deep intimacy) ይጋራሉ፡፡ ቢሆንም ሩካቤ ሥጋ ሕዝብ የሚያየውን ዋጋ ማስከተሉ ደግሞ አይቀርም፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም ሴት በሰውነቷ ላይ ሥልጣን ቢኖራትም የሥልጣኗን ገደብ የማለፍ መብት የላትም፡፡ ሸሉን የማኖርና የመግደል ሥልጣን የእግዚአብሔር እንጂ በጭራሽ የእናቲቱ አይደለም፡፡ ሥልጣን አለኝና በብለላ ፅንሱን ብታስወርድ፣ብዙ ተጠያቂነት አለባት፡፡ አንደኛው ተጠያቂነት እግዚአብሔር የሰጣትን አደራ ያለመወጣት፣ሁለተኛ ነፍስ የመግደልና ሦስተኛው በእግዚአብሔር ሥልጣን ውስጥ እጇን የማስገባት ተጠያቂነት አለባት፡፡ እንደዚህ ያደረገች እናት በምድር ላይ የመንግሥት ሕግ ባይጠይቃትም የሥራዋን ብድራት እየተቀበለች በመጨረሻም አደራውን የሰጣት እግዚአብሔር ለሚጠይቃት ጥያቄ መልስ የምትሰጠው እርሷ ብቻ ትሆናለች፡፡ ያን ጊዜ የዛሬዎቹ አደነጋጋሪ ተከራካሪዎችን አታያቸውም፡፡ ብቻዋን በአምላክ ፊት ትቆማለች፡፡
  4. የማይፈለግ ልጅ ከመወለዱ በፊት ቢሞት ይሻላል፡፡  
    የማይፈለግ ልጅ የሚሉት ምናልባት ያልተሟላ አካል ይዞ የሚወለድ ሊሆን ይችላል፣ወይም እናቱ ስለ እርግዝና ሳታስብና ልጅ መውለድን በማትፈልግበት ወቅትና ሁኔታ ላይ እያለች የተረገዘ ልጅ ሊሆንም ይችላል፡፡ እንዲህ አይነት ልጅ ቢወለድ እናቱ ማሳደግ አትፈልግምና ተወልዶ ከሚሰቃይ ሳይወለድ በፊት እንዲወርድ ማድረግ የተሻለ ነው የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ወላጆች በጥልቅ ድህነት ውስጥ እያሉ ልጅ ተወልዶ ልጁም ወላጆቹም በገንዘብና በምግብ እጦት ከሚሰቃዩ ባይወለድ ለእርሱም ሆነ ለወላጆቹ ምንም ጭንቅ የለባቸውም ይላሉ፡፡ የዚህ አስተሳሰብ መሠረታዊ ችግሮች ብዙ ናቸው፡፡ አንደኛው፣ የአንድን ሰው የወደፊት እጣ ፈንታውን ሌላ ግለሰብ እንዲወስንለት ማድረግ በራሱ አደገኛ አስተሳሰብ ነው፡፡ ሊወለድ ያለ ልጅ የሚፈለግና የማይፈለግ ብሎ ስለ ሌላው የመወሰን መብት ለማንም የለውም፡፡ ከሁሉም በላይ ሰዎች እንዲኖሩ ስላልፈለግን የመግደል መብት ከእግዚአብሔርም ሆነ ከሰው እንዳልተሰጠን በውል ልንገነዘብ ይገባናል፡፡ ይህም የሰው መብት ጥበቃን መርህ የሚጋፋና የሚቃረን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አስተሳሰብ እያደገ ከሄደ ዘር የማጥፋት ፍላጎት ሊጎለብት ይችላል፡፡ ሁለተኛው አሳብ ሽሉን ማንም አይፈልገውም የሚለው አስተሳሰብ በራሱ የተሳሳተ ነው፡፡ ምክንያቱም በሁሉ ሰው የሚጠላ ነገር ሊኖር አይችልም፡፡ በአንዱ የተጠላው በሌላው ይፈለጋል፣አንዱ የሚፈለገውን ሌላው አይፈልገውም እንጂ በሁሉ የሚጠላ ወይም በሁሉ የሚወደድ ሊኖር አይችልም፡፡ ለምሳሌ ብዙ እናቶች ማርገዛቸውን ይጠሉና ልጅ ከተወለደ በኃላ ለልጁ ደጎች ይሆናሉ፡፡ ልጁ እንዲወለድ እናቱ አትፈልግም ማለት ደግሞ እናት ያንን ልጅ አታፈቅረውም ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ትንሰፈሰፍለታለች እንጂ፣ ካልሆነማ በውስጧ ሰብአዊነትም ሆነ ህሊና የለላተት የጌታም መንፈስ የማይገዛት ምናልባትም ነፍሰ ገዳይ የሆነው፣ የዚህ አለም አምላክ የተባለው የዲያብሎስ መንፈስ አድሮባት ሊሆን ይችላል፡፡ የሰውን የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ የሚወስነው የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት እንጂ የሰዎች የግል ምኞት ያፈለቀው ስሜት ሊሆን አይችልም፡፡ ሰዎች በእግዚአብሔር ሉዓላዊ ውሳኔ ላይ እጃቸውን ማስገባት በእርሱ ላይ መድፈር ነው፡፡ እግዚአብሔር መኖርንና አለመኖርን፣ ሕይወትንና ሞትን፣መቻልንና አለመቻልን የሚወስን ሉዓላዊ አምላክና ንጉሥ ስለ ሆነ ውሳኔውን ለእርሱና ለእርሱ ብቻ እንተውለት ዘንድ ይገባናል፡፡
    በሰሜን አሜሪካ ውስጥ ካሉ ትላልቅ ቤተክርስቲያናት አንዱ በሆነው የምታገለግል አንዲት ሴት በአንድ ወቅት ከአቅሟ በላይ የሆነ ነገር ገጠማት፡፡ ከባለቤቷ ጋር የተጋቡት ገና ታዳጊነታቸውን ጊዜ እንደጨረሱ ሲሆን አንድ ልጅ ብቻ እንደወለዱ ባለቤቷ ሞተ.፡፡ ልጁ ግን አንዳንድ ጊዜ አስቸጋሪ ባሕሪያት የሚታዩበት ነውና እናቱ በጣም ትቸገር ነበር፡፡ በሁኔታው እየተቸገረች ባለችበት ወቅት አንድ ቀን ምሽት ጎረምሳ ልጇ አስገድዶ ደፈራት፡፡ በጉዳዩ በጣም ልቧ ተሰብሮ እያለ ከአንድ ወር በኃላ ይባስ ብሎ ማርገዟ ይታወቃታል፡፡ በዚያን ጊዜ የምትሆነው ይጠፋትና ስታወጣ ስታወርድ፣ በእግዚአብሔርም ፊት ስታለቅስ ቆየችና ጭንቀቷን መሸከም ሲያቅታት ጉዳዩን ወደ ቤተክርስቲያን ወሰዳ ለአገልጋዮች በግልጽ አጫውታ የፀሎትና የምክር ድጋፍ ማግኘት እንደለባት ተሰማትና ሄዳ ያለችበትን ሁኔታ በዝርዝር ነገረቻቸው፡፡ የልጇን መጥፎ ሁኔታ ሁሉም ስለሚያውቁ በጣም አዘኑ፣ሊያጽናኗትም ሞከሩ፡፡ ቀጥለውም እንደተሰማቸው መንፈሳዊ ምክር ለገሱላት፡፡ እንግደህ በእንደዚህ ዓይነት አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ላለ ሰው መንፈሳዊ ምክር መስጠት በጣም ከባድ ፈተና ነው፡፡ ለ20 ዓመታት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ባገለገልኳቸው ዘመናት ውስጥ ይህንን የሚያክል ከባድ ነገር ባይገጥኝም ለምክር የሚያስቸግሩ ጉዳያቸውን ይዘው እኔጋ የመጡ ብዙ ምክር ፈላጊዎች እንደነበሩና በእጅጉ የተቸገርኩባቸውን ሁኔታዎች በደንብ አስታውሳለሁ፡፡ ይህቺንም ሴትዮ እነዚያ አገልጋዮች እንዴት አድርገው እንደሚያማክሩአት ግራ ገብቶአቸው ሊሆን ይችላል፡፡ የሆነው እንዲህ ነው፡፡ የአገልጋዮቹ ምክር ለሁለት የተከፈለ ሲሆን ገምሶቹ ይህንን ኃጢአት ወደሽና ፈቅደሽ ያደረግሺው ስላልሆነ ከልጂሽ ወልደሽ ዕድሜ ልክሽን ከምታዚኚ ሕጸኑን ማስወረድ በእግዚአብሔር ዘንድ አያስጠይቂሽም ሲሉ፣ ገምሶቹ ደግሞ የለም፣  ተገድደሽ ስትደፈሪ ኃጢአቱ የአንቺ አልነበረም፣ሕጸኑን ብታስወሪጂ ግን በእግዚአብሔር ፊት በነፍሰ-ገዳይነት ትጠየቂያለሽ፡፡ ልጅሽ ሲደፍርሽና አንቺም ስታረጊዢ እግዚአብሔር ስላየ ፣ ይህንንም ሁኔታ ስለ ፈቀደ ፍርዱን ሉዓላዊ ለሆነው ለእርሱ ብቻ መተው ይኖርብናል እንጂ ጽንሱን እንዳታስወሪጂ ይሉአታል፡፡ ወጥነት ከሌለው የአገልገጋዮቹ ምክር የተነሳ ሴትዮዋ በበለጠ ጭንቅ ውስጥ ብትገባም ወደ ቤቷ ሄዳ በእግዚአብሔር ፊት በመራራ ልቅሶ አምላኳን ስትማጠን የጌታ መንፈስ ሕፃኑን እንዳታስወርድ ተናገራት፡፡ እንግዲህ ለምትወልደው ልጅ እናትም አያትም የመሆን ዕድል ሊገጥማት ነው፣ በሕብረተቡም ዘንድ ልትሳቀቅ ነው፡፡ ይህ እንዴትና ምን ያህል ከባድ እንደሚሆን መገመት ለማንም አያዳግትም፡፡ቢሆንም ሴትዮዋ ከመንፈስ ቅዱስ ድምጽ ጋር ተስማማችና ሕጻኑን ወለደች፡፡.በህብረተሰቡ ዘንድ ያላትን ግምት ወደ ጎን ትታ፣የሚሰማትንም የበታችነት ስሜት ችላ ብላ ልጇና የልጅ ልጇ የሆነውን ፍጥረት ማሳደጉን ተያያዘችው፡፡ የሚገርመው ግን ያ ልጅ አድጎ እግዚአብሔር በኃይል የሚጠቀምበት አገልጋይ ሆነ፡፡ እንግዲህ ሁሉንም ልዑል ለሆነው እግዚአብሔር እንተውለት እንጂ የእርሱን ቦታ በመያዝ የራሳችንን ውሳኔ አንስጥ፡፡ እግዚአብሔር ከመጥፎና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ መልካም ነገርን ማፍለቅ ይችላልና፡፡ ውይይታችንን እዚህጋ ገታ እናድርግና ውርጃን በሚመለከት መጽሐፍ ቅዱሳዊና ነገረ -መለኮታዊ ትንተና ይዘን በሚቀጥለው ክፍል እንመለስበታን፡፡

1Joel R. Beeke. Is Abortion Really so Bad?. Pasadena, California: Chapel Library,2011 pp.1-3
2Jane English. Abortion and the Concept of a Person.1984, p.153.
3Joel R Beeke , Is Abortion Really  So Bad?, p.4
4Ibid.,p.5