Monday, May 26, 2014

 ምድራችሁን እፈውሳለሁ (ክፍል ሦስት)                                                                                                           
                                                                                              ፓስተር ሳሙኤል ሾንጋ
ምድራችሁን አፈውሳለሁ ይላል እግዚአብሔር በሚል ርዕስ ለሁለት ተከታታይ ጊዜያቶች በጣም ሰፋ ባለ መልኩ በብዙ ነጥቦች መነጋጋራችን ይታወሳል፡፡ በሁለቱም ክፍለ ውይይት በምድራችን ለሚታየው መንፈሳዊ ሕይወት ችግሮች ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ስናደርግ የቆየነው የቤተ ክርስተያናችንን ተቀዳሚ መሪዎች በተለይም በአሜሪካን አገር የሚገኙ ፓስተሮችንና ነቢያትን እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ይሁን እንጂ እነርሱ ብቻ መወቀስ አለባቸው ወይ የሚለውን ጥያቄ ማንሳት ይኖርብናል፡፡ እውነት እንነጋገር ካልን መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ሁላችንም በአንድነት ተሳስተናል፡፡ መሪዎችን የወቀስነው መልካም ምሳሌ መሆን ስላልቻሉ ነው እንጂ ሁላችንም ጋ ችግር አለ ፡፡ ሕይወታቸው ወደ ሕብረትና ወደ ቅድስና ፣ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራት ስለማያሳየን ነው እንጂ ኢትዮጵያውያን የሆንን አማኞች ሁላችን አሁን ለሚታየው ውድቀት ተጠያቂዎች ነን፡፡ እያንዳንዱ በእግዚአበሔር ፊት የሥራውን ዋጋ ይቀበላል፡፡ ወንድም እገሌ ወይም ፓስተር እገሌ አሳስቶኝ ነው ብሎ ሊያመልጥ የሚችል አንድ የለም፡፡
የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ባቆሸሽንበትና ለብዙዎች እንቅፋት በሆንንበት ሁሉ ንስሐ መግባት ይኖርብናል፡፡ ጉዳዩ ሁላችንንም የሚመለከት ነው፡፡ መንጋውን በፍቅርና በትጋት እንደ እግዚአብሔር ቃል መሠረት ያልመራን መሪዎች(ሽማግሌዎችና ፓሰስተሮች)፣ ከጌታ የተቀበልነውን ሕዝብ በእውነተኛው እግዚአብሔር ቃል ኮትኩተን ያላሳደግን መጋቢዎች፣ ወንጌል የመዳረስን ኃላፊነት ያልተወጣን ወንጌላውያን፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ያልሆነውን ትንቢት በመናገር ምዕመናንን ያደናገርን ነቢያት፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለእግዚአብሔር ቃል ታማኝ ያልሆን ምዕመናን፣ መዘመራን በተለይም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑትን ምድራዊ ዝማሬዎችን ብቻ በመግጠም ሕዝቡን ወደ ሰማዊ እውነት ለማመልከት ያቃተን መዘምራን ሁላችንም በአንድነት ወደ እግዚአብሔር መመለስ በሚያስፈልገን ወሳኝ ወቅት ላይ መሆናችንን ልንገነዘብ ይገባናል፡፡
ይህንን ያህል ካኩ በኋላ እየተነጋርበት ወደ ነበረው አሳብ መመለስ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ምድርን ለመፈወስ ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በዝርዝር ስንመለከት ቆይተናል፡፡ እነርሱም ፡ ሰውነትን በማዋረድ በንስሐ መጸለይ፣ ከክፉ መንገድ ወይም ከኃጢአት መንገድ መመለስ ሲሆኑ እነዚህን መድረግ የሚጠበቅብን በእግዚአብሔር ስም የተጠራን የእርሱ ሕዝቦች መሆናችንን በ2ኛ ዜና 711-14 በላው ክፍለ ንባብ ተመልክተናል፡፡ በዚህኛው ክፍል ደግሞ ስለ ሦስተኛው ነጥብ እመለከታለን፡፡
3. የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ፡
የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ለክርስና ሕይወትና ከእግዚአብሔር ጋር ለሚኖረን ሕብረት እጅግ በጣም ወሳኝ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው ይላል (መዝ.1054)፡ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ማለት ምን ማለት ነው? እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት የእርሱን ህዉና መናፈቅ ማለት ነው፡፡ ህልውና ስንል presence የሚባለውን ነው፡፡ ይህ በብራውያን ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ ህውናውን መፈለግ ማለት በፊቱ መገኘት እንደማለት ይቆጠራል፡፡ እንግዲህ የእግዚአብርን ፊት ወዴት ብን ነው የምንፈልገው; እርሱ በሁሉ ቦታ የሚገኝ (Omnipresent) የሆነ አምላክ ነው፡፡ እርሱ መንፈስ ነው እንዴት አድርገን ነው የምንፈልገው? ተፈልጎስ የሚገኝ አምላክ ነው ወይ? እርሱ ሁሉንም ነገር በሥልጣኑ ይገዛዋል የቆጣጠረዋልም፡፡ ከዚያም አልፎ ለእኛ ለእያንዳንዳችን ቅርብ የሆነ አምላክ ነው፡፡ ታዲያ እንዴት ነው የእርሱን ህልውና ወይም ፊቱን የምንፈልገው? እንግዲህ እርሱ በቃሉ ፈልጉኝ ያለው ይህንን ሁሉ እያወቀ ነው፡፡
የማቴዎስ ወንጌለ 2020 ስንመለከት እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ ብሏል፡፡ ከዚህ ቃል ኪዳን የተነሳ ህልውናው ሁል ጊዜ ከልጆቹ ጋር ነው፡፡ በመከራ ጊዜ ያግዘናል፣ ስንወድቅ ያነሳናል ስንደክም ያበረታናል፣ በአጠገባችን ሆኖ በሁሉም አንጸር ልባችንን ይደግፍልናል፡፡ ይህ የቅርብ አምላክ በፊቱ እንድንሆን ዘንድ ይፈልጋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ እግዚአብሔርን እንድንፈልግ ይጠይቀናል፡፡
የብሉይም ሆነ የአዲስ ኪዳናት እንደሚያብራልን እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት አንድ የፋብንን ነገር ለማግኘት የሚናደርገው ዓይነት ትግል አይደለም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር አልጠፋብንም፡፡ ድርምና በግ የጠፋባቸው አጥብቀው በፈለጉበት መንፈስና አእምሮ እርሱን አንፈልገውም፡፡ እግዚአብሔርን መፈለግ ስንል አንድ የጠፋብንን ነገር ለማግነት በምንበረብርበት አኳኋን እርሱን እንፈልገዋን፡ ለምሳሌ በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 3-10 ባለው ቦታ የጠፋባቸውን ነገር የፈለጉ ሰዎችን እናገኛቸዋለን፡፡ አንደኛው በግ የጠፋት ሰው ሲሆን ይህ ሰው አንዱን በግ ለመፈለግ ዘጠና ዘጠኙን ሜዳ ይ ትቶ አንዱን በግ ለመፈለግ ሄደ፡፡  ሌላ ደግሞ ድሪም የጠፋባት ሴት መብራት አብርታ ቤቷንም ጠርጋ እክስታገኘው ድረስ እንደምትፈልገው ጌታ አስተማረ፡፡ የጠፋው በግ የተገኘው ወደ ዱር በመሄድ ወይም እውጭ በመውጣት አለያም በጉ ወደ ኮበለለበት አገር ሁሉ በመሄድ ነው፡፡ ድሪሙ የሚገኘው ደግሞ ሩቅ ሳይከድ እቤት ውስጥ መብራት በማብራትና ቤትን በመጥረግ ነው፡፡ አንዳንድ ነገር ሩቅ ተክዶ ይገኛል፣ አንዳንዱ ግን እዚያው እያለ የጠፋ ስለሆነ የሸፈነውን ነገር በመግለጥ ይገኛል፡፡ እንግዲህ መፈለግ ማለት ይህ ከሆነ እግዚአብሔርን ለማግኘት የምንፈልገው ሩቅ አገር በመሄድ ነው ወይስ አካባቢን በማጽዳት ነው? እግዚአብሔርስ ፈልጉኝ ሲል አንድ ቦታ ተደብቆ ከእኛ ጋር አኩኩሉ እየተጫወተ ነው ማለት ነው? እርስ አውቆ ተደብቆ እኛን ፈልጉኝ እያለ እያደከመን ነው ማለት ነው ወይስ እግዚእሔርን እንፈልግ ስንል እንዴት ነው የምንፈልገው?
እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት ከዚህ ሁሉ የሚለይ ነው፡፡ ነገር ግን ልባችንንና አእምሮአችንን እግዚአብሔርን ለማወቅ የማዘጋጀት ሂደት እንደሆነ ያስተምሩናል፡፡ አሁንም እግዚአብሔርን ትፈልጉ ዘንድ ልባችሁንና ነፍሳችሁን ስጡ( 1 ዜና 2219)፡፡ ልብን መስጠት ማለት አውቀንና ወደን ልባችንንና አስተሳሰባችንን ለእግዚአብሔር ማስወረስና ወደ እርሱ መመለስ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ በተሰሎንቄ ላሉ አማኞች ሲጽፍ ጌታም ወደ እግዚአብሔር ፍቅር ወደ ክርስቶስም ትዕግሥት ልባችሁን ያቅናው(2 ተሰ 35) ይላቸዋል፡፡ እርሱን መፈለግ ማለት ከፍጹም ነፍሳችንና ልባችን ፈቃዱን፣ ፍቅሩን ፣ ሪህራኄውን፣ ምህረቱን፣ ቸርነቱንና ጸጋውን መሻትና መናፈቅ ማለታችን ነው፡፡ መፈለግ ማለት እንዲህ ከሆነ እርሱን ለማግኘት የትም ሩቅ መሄድ አያስፈልግም ምክንያቱም አምላካችን በአጠገባችን ከዚያም በቀረበ መልኩ በውስጣችን ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ፊቴን ፈልጉ ሲል ጌታ የሚፈልግብን ይህንን እንጂ ሌላ አድካሚ መንገድ እንድንሄድበት አይደለም፡፡ ስለዚህ ምድራችን እንድትፈወስ ሁላችንም የእግዚአብሀየርን ፊት ልንፈልግ ይገባናል፡፡ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ የሚለው ቃል ምን እደሀነ የሚገባቸው ያመኑና በስሙ የተጠሩ ሰዎች ናቸው፡፡ እግዚአብሄርም ራሱ ፊቱን እንዲፈልጉ የሚጠብቅባቸው በስሙ የተጠሩትን ሰዎች ነው፡፡ ስለዚህ በሄ ክርሰቲያን የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግን ልማድዋና ባህልዋ የምታደርግ ከሆነ በእርሷ ምክንያት ምድራችን ትፈወሳለች፡፡ ስለዚህ ለሁላችንም የቀረበ አስደናቂ መልእክት ይህ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በልጁ በኢየሱ ክርስቶስ በኩል እንደ ባለጠግነቱ መጠን በሚያስፈልገን ነገር ሁሉ ይሙላብን ፡፡ እንደ ተስፋ ቃሉም ምድራችንን የፈውሳት ፡፡ አሜን፡፡





No comments:

Post a Comment