ፓስተር
ሳሙኤል ሾንጋ
ሕያው
ፍጡር በሆነ በተለይም በሰዎችና በእንስሳት
ሁሉ ከሚታይ ስሜት አንዱ ፍርሃት ነው፡፡
የዓለም ጠበብት የፍርሃት ዓይነቶችን
በተለያየ
መልክ ያስቀምጡታል፣ ይገልጹታልም፡፡ ፍራስቴር
ኬንት የተባሉ እውቅ ፀሐፊ “nothing
to fear” 1977 Doubleday and Company በተሰኘው
ጽሑፋቸው ካሰፈሩት ጥቂቶቹን ለመግለጽ ያህል
ፔላዶፊያ የሚባለው የፍርሃት
አይነት አለ፡፡ ይህ ዓይነቱ ፍርሃት የጸጉር
መመለጥና ጸጉራቸው የተመለጠ ሰዎችን መፍራት
ነው፡፡ ኤሮፎቢያ የሚባለው ደግሞ ሊመጣ ያለውን
ረሀብ ወይም ድርቅ እያሰቡ መጨነቅን የሚያመለክት
ሲሆን ቻዬቶፎቢያ በመባል የሚታወቀው ፍርሃትም
አለ፡፡ ይህ ደግሞ ጸጉራም ሰዎችን መፍራት
ሲሆን ፔላዶፊያ የተሰኘው ተቃራኒ ነው፡፡
በስተግራ በኩል ስላሉ የአካል ብልቶቻችን
እያሰቡ መጨነቅና መፍራት ሌቮፎቢያ የሚባለው
ሲሆን በተቃራኒው ስለ ቀኝ የአካል ብልቶች
እያሰቡ መጨነቅና መፍራት ዴክስትሮፎቢያ
ይባላል፡፡ ይህ ማለት ጉበቴ ታሞ ይሆን ፣
ሳምባዬ ቆስሎ ይሁን ፣ ኩላሊቴን
ካንሰር ይዞት
ይሆን በማለት አሳብን በማውጣትና በማውረድ
አእምሮን በፍርሃት መሙላት ማለት ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ ወደ ሐኪም ቤት ሄዶ ለመመርምር
ሰፊ ዕድል እኳን እያለ ያንን ወደ ጎን ትተው
ስለ ሕመም የሚፈሩ ሰዎች ሌቮፎቢያና ዴክስትሮፎቢያ
ያጠቋቸው
ናቸው፡፡ ምንም ሳያማቸው እንዲያው ከመሬት
ተነስተው ሊያመኝ ነው መሰለኝ ብለው ቤተሰብና
ጎረቤትን የሚያሸብሩ ሰዎች
ጥቂት አይደሉም፡፡ በዚህ ብቻ ሳያበቃ ሌላ
ደግሞ ካሊፕሮፎቢያ የሚባል የፍርሃት ዓይነትም
አለ፡፡ ይህኛው ደግሞ ስለ ሥውር ወይም ድብቅ
ስለሆኑ ነገሮችና ስለ ትርጉማቸው እያሰቡ
መፍራት ነው፡፡ አውሮራፎሪያ የሚባለው የሚገርም
የፍርሃት ዓይነት ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ፍርሃት
ስለ ሰሜናዊ ብርሃናት እያሰቡ መፍራት ነው፡፡
ለእንዲህ ዓይነት የተጋለጡ ሰዎች ሌሊት ሲሆን
በሰሜን ዋልታ አካባቢ ከርቀት የሚታዩትን
ብርሃናትን ይፈራሉ፡፡ እነዚህ ብርሃናት
ምንም የሚያደርጉ ባይሆኑም የሚያዩ ሰዎች
ግን ዝም ብለው ይፈሩአቸዋል፡፡ የሚገርመው
ፍርሃት ደግሞ ስታብስባስፎቢያ የሚባው ስለ
መቆምና ስለ መሄድ መፍራት ነው፡፡ ሰዎች
በአንድ ሥፍራ ለመቆም
ይፈራሉ ከዚያ ቦታ ስለመንቀሳቀስም ይፈራሉ፡፡
እዚያ ጋ ቁም ሲባሉ እፈራለሁ፣ ተንሳቀስ
ሲባሉም እፈራለሁ የሚሉ ሰዎች ያለባቸው ችግር
ሲሆን ይህ ዓይነቱ ግራ የሆነው
የሆስታብስባስፎቢያ ተብሎ
ተሰይሟል፡፡ በሕዝብ ፊት አንድን ነገር ለመጻፍ
እፈራሁ የሚሉ ሰዎች ያሉ ሲሆን እነዚህ ሰዎች
ያላቸው ፍርሃት ጋራፎፎቢያ የሚባለው ነው፡፡
ፍርሃትን
ራሱን መፍራት ደግሞ ያለ ሲሆን እሱኛው ፎቦፎቢያ
ተብሎ ያጠራል፡፡ እነዚህና የሚመስሉ ሌሎችም
የፍርሃት ዓይነቶች ያሉ ሲሆን እነዚህ ሁሉም
ምንም የተጋባቸው ፍርሃቶች ሳይሆኑ አላስፈላጊ
ፍርሃቶች ናቸው፡፡
ፍርሃት
በሰው ሕይወት ለምን ይፈጠራል ማለት አንችልም፡፡
በእርግጥ የሚያስፈሩ ነገሮች ስላሉ ለመፍራት
እንገደዳለን፡፡ የሚነድ እሳት ስናይ፣የከባድ
መሣሪያ ፍንዳታ ስንሰማ በውስጣችን የሚፈጠረው ፍርሃት ተገቢና
ኃጢአት የሌለበት ነው፡፡ የመኪና መንገድ የሚያቋርጥ አንድ ሰው ከላይና
ከታች የሚተምሙትን አዎቶሞቢሎችና ካሚዮኖችን
ሲያይ ልቡ በጣም ይፈራል፡፡ ያየው ነገርና
ያለበት ቦታ እንዲፈራ ያስገድደዋል፡፡ ነገር
ግን ነገ ምድር ብትናወወጥ ምን እሆናለሁ ፣
ልጆቼንስ በምን ውስጥ እሰውራለሁ?
ወይም
ከአዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የሞቱና በመቃብር
ውስጥ ያሉ ሰዎች ቢነሱ ምድር እንዴት ትበቃለች
በሚል እያሰበ እንቅልፉን እንዳጣ ሰውዬ ዓይነቱ
ፍርሃት ምን ይባላል?
የእግዚአብሔር
ቃል እንዳንፈራ በተደጋጋሚ ይናገራል፡፡
በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን አትፍሩ
የሚል የማጽናኛ ቃል በብዙ ቦታ እናገኛለን፡፡
እግዚአብሔር አትፈሩ የሚለን እንደምንፈራ
ስላወቀ ነው፡፡
ስለፈራችሁ ከእግዚአብሔር ጋር ምንም እድል
ፋንታ የላችሁም አልተባልንም፡፡ ታላላቅ
ተአምራን ያደረጉ የብሉይ ኪዳን ታላላቅ ሰዎች
መፍራት በማይገባቸው ሁኔታ ፈርተዋል፡፡
የእግዚአብሔር ሰው ነቢዩ ኤልያስ ኤልዛቤልን
ፈርቶ አንድ ቀን ሙሉ መንገድ
እንደሮጠ በቃሉ እናነባለን፡፡
የሲዶናውያን ንግሥት ኤልዛቤል በኤልያስ
አገልግሎት ስምንት መቶ አምሳ ነቢያቶችን
በማጣቷ ስለተቆጣች
ነገ በዚህን ሰዓት ከእነዚህ ነቢያት እንደ
አንዱ ነፍስ ባላድርግብህ አማልክት ይህንን
ይጨምሩብኝ ስትለው ነፍሱን ለማዳን ሮጠ፡፡
ከአንድ ቀን በፊት ግን ከበዓል ነቢያት ጋር
በአምላኩ ስም ተወራርዶ ከሰማይ እሳት ካዘነበ
በኃላ 450 የበዓል
ነቢያትን አሳርዶ ነበር፡፡ ነገር ግን ኤልዛቤልን
ዛቻ ሲሰማ ነፍሱን ለማዳን ሮጦ ሲደክመው
ከክትክታ ዛፍ ሥር ሆኖ እኔ ከቀደሙት አባቶቼ
አልበልጥምና ነፍሴ ውሰድ ብሎ የጸለየው
ከፍርሃት የተነሳ ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ጸሎት
ትክክለኛ ጸሎት ሳይሆን ፍርሃት የወለደው
ነው፡፡ ኤልዛቤል ስትዝትበት
ትናንት በእርሱ ጸሎት እሳት ያወረደውን ጌታ
እዛው ባለበት ቦታ ሆኖ መጠየቅ እንዴት
እንደጠፋበት ያስገርማል፡፡ እግዚአብሔርን
ከመጠየቅ መሮጥ የሚያዋጣው መስሎት ይሆን?
አናውቅም፡፡
አንዳንድ ጊዜ የምንጸልያቸው
ትክክለኛ ያልሆኑና በውስጣችን ያለው ፍርሃት
የሚያመነጫቸው ጸሎቶች አሉ፡፡ ኤልያስ በዚህ
ጊዜ እግዚአብሔርን ግደለኝ የሚለው ከልቡ
ሞት ፈልጎ ነው ማለት ያስቸግራል ምክንያቱም
የአንድ ቀን መንገድ ሮጦ የመጣው ከሞት ለማምለጥ
ነውና፡፡ የሚጠይቀው በእርግጥ ለመሞት ከሆነም
እግዚአብሔርን ግደለኝ ከሚል ይልቅ ኤልዛቤል
ጋ መሄድ ነበረበት፡፡ እገድላለሁ ያለቺው
ሴት እዛው እያለች እርሷን ሸሽቶ መጥቶ በሕይወቱ
ትልቅ ሥራ ለመሥራት የመረጠውን እግዚአብሔርን
ግደለኝ ማለቱ ከመፍራቱና ከመጨነቁ የተነሳ
የተናገራቸው አሳቦች ናቸው፡፡ እንግዲህ ስው
ሁሉ ፍርሃት አለበት፡፡ ሐዋሪያው
ቅዱስ ጳውሎስ በሕይወቱ ስለ ገጠሙት ፍርሃቶችና
የፍርሃት ምክንያቶች
ሲገልጽ በወንዝ
ፍርሃት፣ በመንገድ ፍርሃት፣ በወገኔ በኩል
ፍርሀት ፣ በአህዛብ በኩል ፍርሃት፣ በከተማ
ፍርሃት ፣ በምድረ በዳ
ፍርሃት፣ በባሕር ፍርሃት ፣ በውሸተኞች
ወንድሞች በኩል ፍርሃት ነበረብኝ (2
ቆሮ.
11፡26)
ብሏል፡፡
ሐዋሪያው
ጴጥሮስም የማዕበሉ ጌታ የሆነ ኢየሱስ በአጠገቡ
እያለ እንኳን ፈራ፡፡ የማይፈራ ሰው አንድም
የለም፡፡ እንዲያውም እግዚአብሔር ቃል
በተደጋጋሚ አትፍሩ የሚለን ስለምንፈራ ነው፡፡
የማይፈራውን ሰው አትፍራ የሚለው የለውም፡፡
ልጆቻችንን አትፍሩ የምንላቸው መፍራታቸውን
ስናይ እንጂ እንዲሁ ከመሬት ተነስተን አትፍሩ
አንላቸውም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ትንቢት
በተናገሩ ነቢያቶችም ሆኑ መልእክት በጻፉልን
ሐዋሪያት በኩል በተደጋጋሚ አትፍሩ የሚል
መልእክት የተሰጠን እግዘአብሔር መንቦቅቦቃችንን
ስላወቀልንና ስለተረዳልን መሆኑ የሚያጠራጥር
አይደለም፡፡
እግዚአብሔር
አምላክ የእርሱ የሆኑትን አትፍሩ እያለ
የሚያጽናናበትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሁሉ
በአንድ ጊዜ ማየት አንችልም፡፡ ለአሁኑ ግን
ለምን መፍራት እንደለለብን በትንቢተ ኢሳያስ
43፡1-7
ያለውን
ክፍል
እመለከታለን፡፡ በዚህ
ክፍል የጌታ ቃል አትፍሩ እያለ ሁለት ጊዜ
ይናገራል(ቁ.1
እና ቁ
5)፡፡
እጅግ በጣም አስፈሪ በሆኑ በሁኔታዎች
ውስጥ ብናልፍም
እንኳ ጌታ
አትፍሩ ይለናል፡፡ በዚህ የንባብ
ክፍል በሰዎች ልጆች ሕይወት በአስፈሪነታቸው
አቻ የማይገኝላቸው ሁለት ነገሮች እንደ ምሳሌ
ቀርበዋል፡፡ አንዳኛው ውሃ ሲሆን ሁለተኛው
እሳት ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱም ለሰው ልጆች
ጥቅም የሚሰጡ ቢሆኑም ከልኩ ካለፉ ግን አስፈሪዎች
ናቸው፡፡ ውሃ በምንጠጣው፣ በምንታጠበው፣
ምግባችንን በምናበስለውና እርሻችንን በምለማው
ወዘተ ልክ ሲሰጠን እንጂ ከዚያ ካለፈ ግን
አደገኛ ነው፡፡
ከልኩ ያለፈ ውሃ ለመቆጣጠር የማይቻለውን
ጥፋት ያስከትላል፡፡ በጃፓን አገር የነበረው
የሱናሚ አደጋ ስናስብ ውሃ ያንን የሚመስለውን
አገር ለማውደም ምንም
ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ እንደ
አውሮጳውያን አቆጣጠር 2011 ላይ
በተከሰተወ ረእደ- መሬትና
የውሃ መጥለቅለቅ 125 ሺህ
ቤቶች ተጠራርገው ተወስደዋል፡፡ በጊዜው
የወደመው ንብረት በ310 የቢሊዮን
የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው፡፡ ይህ የውሃ
ጥፋት ከንብረት በላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ
ሰዎችን ሕይወት አጥፍቷል፡፡ በጃፓን ምሥራቅ
ጫፍ ላይ የተነሳው የጎርፍ አደጋ መኪናዎችን፣
ጀልባዎችን ካሚዮኖችን፣ እንዲሁም ደግሞ
መኖሪያ ቤቶችን ሲያገኛቸው ሁሉም እንደ ቅጠል
እየተንሳፈፉለት ተጠራርገው መድረሻቸው
ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል፡፡
ውሃ በእጥፊነቱ የሚታወቅ እንደሆነ
የእግዚአብሔርም ቃል ይነግረናል፡፡ እግዚአብሔር
በምድር ላይ የወጣውን የሰውን ጥፋት ሲያይ
ምድርን የቀጣው በጥፋት ውሃ ነበር(ዘፍ.7)፡፡
ያ የጥፋት ውሃ ወደ መርከብ ውስጥ የገቡት ብቻ
ሲቀሩ በምድር ላይ ያሉትን ተንቀሳቃሾች ሁሉ
አጠፋ፡፡ እግዚአብሔር የእሥራኤልን ሕዝብ
ከግብጽ ባሪነት ነፃ ያወጣበት ጊዜ በግብጻውያን
ላይ ያደረገው
የመጨረሻው ቅጣት በውሃ እንዲወሰዱ ማድረግ
ነበር፡፡ ውሃ የሚያስከትለው
ጥፋት ከፍተኛ
ነው፡፡ ዳዊት እግዚአብሔር እንዴት አድርጎ
ጠላቶቹን
እንዳፈረሰለት ሲመሰክር ውሃ እንዲያፈርስ
እግዚአብሔር
ጠላቶቼን በእጄ አፈረሳቸው ሲል ያንን ሥፍራ
ኤልፐራሲም አለ( 2
ሳሙ.5፡20).፡፡
ይህ ማለት ውሃ ትላልቅ ግንቦችን ለማፍረስ
የሚችልበት ኃይል ያለው መሆኑን የሚያመለክት
ነው፡፡ ነቢዩ ናሆምም እግዚአብሔር
በጠላቶቹ ላይ መዓቱን ሲልክ በሚያጥለቀልቅ
ጎርፍ እንደሚያስወስዳቸው ተናገረ(
ናሆም
1፡5-9)፡፡
እሳትም
በምንሞቀው ልክ፣ እህላችንን በምናበስልበት
ልክ፣ እንዲሁም የአካባቢያችንን ቆሻሻ በማቃጠል
በማስወገድ በምንችልበት ልክ ብቻ ሲሰጠን
በጣም ይመቸናል፡፡ ከዚያ በዘለለ መልኩ ከከልሉ
የወጣ እሳት እጅግ በጣም የሚያስፈራና
በቃል ሊገለጥ የማይቻል ጥፋትና ውድመት
ሊያደርስ
የሚችል ነገር ነው፡፡ የእግዚአብሔርን
የፍርድ ጥልቀት ለማሳየት መጽሐፍ ቅዱስ ከእሳት
ጋር ያመሳስለዋል፡፡ እግዚአብሔርን
ራሱን የሚባላ እሳት ነው ይለዋል(
)፡፡
የመጨረሻውና ከባዱ የእግዚአብሔር ፍርድ
የሚከናውንበትን ሁኔታ ከእሳት ጋር ያያይዘዋል(
ገሀነመ
እሳት ወይም የእሳት ባህር በማለት)፡፡
እሳት የበላውን ነገር መልሶ ለምንም ነገር
ማዋል በጣም አስቸጋሪ ይሆናል፣
አይቻልምም፡፡ እሳት አንድን ነገር ከነበረበት
ሁኔታ በአጭር ደቂቃዎች
ውስጥ ወደ አመድ ሊለውጥ ይችላል፡፡ ቤቶችን
እንዳልነበሩ
ለማድረግ ምንም ጊዜ አይወስድበትም፡፡ በአለም
ሥልጣኔ ትልቁን ሥፍራ የምትይዘውን አሜሪካንን
በየዓመቱ
የሚፈታተን ነገር ቢኖር የዱር
እሳት /wild fire/ የሚባል
ነው፡፡ ይህ እሳት
ሲነሳ በተለይም በበስተ ደቡብ ምዕራብ አካባቢ
ያሉ ደኖችን
እንዳልነበረ
ያደርጋቸዋል፡፡
የግዙፍ ሥልጣኔ ባለበት የሆነቺው አሜሪካ
ይህንን ለመከላከል ምንም ግኝት የላትም
፡፡ሳያስቡት
ቀርተው ሳይሆን
ያንን ማግኘት አሰልቺም አድካሚም ስለሚሆንባቸው
ሊሆን ይችላል፡፡
ከሥልጣኔ ጋር በተያያዘ በምጣኔ ሀብት የበለጸጉ
አገሮች የመብረቅ መከላከያ የመሳሰሉ ነገሮች
አሉአቸው ፣ አዳጊ አገሮችም ይህን እየተጠቀሙበት
ነው፡፡ ግን እሳትና ውሃን እንዲሁም
የሚያስከትሉአቸውንም
ጥፋት ለመመከት
ምንም መከላከያ የላቸውም፡፡ የእሳት አደጋ
ቢርጌድ የሚባል ቢኖርም የተወሰኑ ትናንሽ
ቃጠሎዎችን ከማጥፋት በቀር ሌላ ከዚያ ያለፈ
ነገር ማድረግ አይችልም፡፡
የሚገርመው ነገር እሳት ዓለት
ማቅለጥ ሁሉ ይችላል፡፡ የእሳተ ገሞራ ፍሳሽ
እኮ የአለት ቅላጭ ነው፡፡ ታዲያ እሳት ይህን
ያህል አቅም ያለው ከሆነ አደገኛነቱና አጥፊነቱም
ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፡፡
እግዚአብሔር
በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል ለሕዝቡ ያስተላፈላቸው
መልእክት በእሳት ውስጥ እያለፉ እንደማይቃጠሉ፣
በውሃም ውስጥ ሲሄዱ እንደማይሰምጡ የሚያረጋግጥ
ነበር፡፡ በውሃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ
ጋር እሆናለሁ፣በወንዞች ውስጥ ባለፍህ ጊዜ
አያሰጥሙህም፣ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ
አያቃጥልህም ፣ ነበልባሉም አይፈጅህም(
ኢሳ
43፡2)
ይላል፡፡
ይህ አባባል ምን ያህል አስገራሚ ቃል እንደሆነ
እናስብ፡፡ ሰው እንዴት ነው እሳት ውስጥ ገብቶ
የማይቃጠለው? በውሃ
መካከልስ እየሄደ እንዴት አይሰጥም?
በእሳት
ውስጥ ያለ ሰው እንዴት ሆኖ ነው ነበልባሉ
የማይፈጀው? በእውነት
ይህ አስገራሚ የሆነ የእግዚአብሔርን ጥበቃና
እርሱ ለእኛ የሚሰጠውን ዋስትና ያረጋግጥልናል፡፡ አንዳንድ
ጊዜ ሕይወታችን በእሳት ውስጥ እንደማለፍና
በወንዞች መካከልም እንደመራመድ ይሆናል፡፡
ይሁን እንጂ ከዚህ በርካታ አስደናቂ እውነቶችን
እንማራለን፡፡
1.
እሳትና
ውሃ ማለፊያችን እንጂ መኖሪያችን አይደለም፡፡
አዎን በሕይወታችን እንደ እሳት
የሚነድዱና እንደ ውሃ የሚመነቃቅሩ
ፈታኝ ሁኔታዎች ሊፈጠሩብ ይችላሉ፡፡ በዚያ
ሁኔታ ውስጥ እናልፍበታለን እንጂ ዕጣ ፋንታችን
አይሆንም፡፡
ቃሉ በእሳት ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ፣ በሄድህ ጊዜ
ይላል እንጂ እሳቱና ውሃው መኖሪያህ በሆነ
ጊዜ አይልም፡፡ ስለዚህ
እሳቱ ውስጥ መግባታችንን ብቻ አንመልከት፣
በውስጡ አልፈን ወደ ጫፉ ወይም ወደ ዳር
እንደምንወጣም ደግሞ እናስብ፡፡
የማዕበሉና ኃይል ስናይና የእሳቱን ትኩሳት
ስንሰማ እንጨነቃለን፡፡ በዚያ ውስጥ የምናልፍበት
ጊዜው አጥሮልን ለማየትና
ቶሎ ለመገላገል እንቸኩላለን፡፡ ምክንያቱም
ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ጊዜ ሳይሆን በእኛ
ጊዜ እንዲሆንልን
ስለምንፈልግ
ነው፡፡ እግዚአብሔርም በሥጋ ዓይናችን
ስለማይታየን ከውሃው ሙላት፣ ከማዕበሉ ጉልበትና
ከእሳቱ ትኩሳት
ጋር
የምንታገለው እኛው ብቻ ይመስለናል፡፡ ትላንት
እግዚአብሔር እንዴት እንደረዳንና እንዳሻገረን
ሳይሆን ዓይናችን የሚያርፈው
ከፊታችን ሆኖ የሚንቀለቀለው እሳትና በሚገለባበጠው
ወጀብ ላይ ነው፡፡ ስለዚህ መንገዱ የረዘመብን
ስለመሰለን
እንጨነቃለን፣ እግዚአብሔርም የተወን
ይመስለናል፡፡ በቀን 24
ሰዓታት
ብቻ መኖራቸው ለማንም ግልጽ ቢሆንም
መከራን የምንቀበልባት ሌሊት ሰዓቱ የተጨመረ
ይመስልብናል፡፡ አንዳንዴ 2
ሰዓት
ያህል ጊዜ የሁለት ወር ያህል ይረዝምብናል፡፡
ይህ የሚሆነው ቶሎ ነግቶልን ብርሃን ለማየት
ስለምንጣደፍ ነው፡፡ ሌሊቷ ግን በተወሰነላት
መሠረት እንጂ እኛ
ስለ ቸኮልን ብላ ከእኛ ጋር አትጣደፍም፡፡
የሆነ ሆኖ ሌሊቲቱ
ምንም መራራ ብትሆንም ስለ እኛ ብላ ሳይሆን
እንዲትነጋ
በተወሰነላት መሠረት መንጋቷ አይቀርም፡፡
የሚገርመው ግን ያቺ ሌሊት ሰትነጋ ምንም
ሳንሆን ማደራችንን እንገነዘባለን፡፡
በሰላም ያሳደረን የተጨነቅንበት ጭንቀት
ሳይሆን ማዕበሉን የሚቆጣጠር፣ የእሳቱን
ኃይል ውሃ
የሚያደርገውና
ጨለማውን የሚያበራው ጌታ ከልሎን ስለሚያሻግረን
ነው፡፡ እርሱ አሁንም በምንሄድበት
መንገድ ሁሉ ከእኛ
ጋር ሆኖ ያሻግረናል፡፡
2.
እሳቱ
መጥሪያችን እንጂ መጥፊያችን አይደለም፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ወደ እሳት
ውስጥ ሲያስገባን ሊያጠፋን ወዶና አቅዶ
አይደለም፡፡ ነገር ግን በዚያ ሁኔታ ውስጥ
በማሳለፍ የጠራንና ወደ ከበረው የሕይወት
ደረጃ የደረስን እንድንሆን ወዶ ነው፡፡
በአንገታችንና በእጃችን የምናደርገው
ወርቅ እንደዚያ ያማረውና ለሰው ሁሉ እይታ
የሚስብ የሆነው እንዲሁ በቀላሉ ሳይሆን
በእሳት ተፈትኖ ካለፈ በኃላ ነው፡፡ የክርስትና
ሕይወትም እንደ እሳት ተፈትነን
የምናልፍበት መንገድ ነው(
1 ጴጥ.4፡11)፡፡
ወደ እሳት ውስጥ ሳያልፍና ሳይቀልጥ የሚያምር
መልክ ያለው ወርቅ እንደሌለ ሁሉ እግዚአብሔር
ባዘጋጀለት የፈተና
መንገድ ሳያልፍ ወደ ክብርና መንፈሳዊ በረከት
ሊደርስ የሚችል ክርስትናና
የክርስትና ሕይወት ሊኖር አይችልም፡፡ ልብስ
ስንለብስ መልበስ የሚያምረው በውሃ ከታጠበ
በኃላ በካውያ በደንብ ሲተኮስ ነው፡፡ የምንበላው
ምግብም የሚያረካ
ጣዕምና የሚስብ ቃና ወይም ሽታ የሚኖረው
በእሳት የተቀቀለ፣የተጠበሰ ወይም የተቆላ
እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ በእሳት
ውስጥ ማለፍ ወደተሻለና ወደሚፈለግ ማንነት
ያሸጋግረናል፡፡
3.
እግዚአብሔር
እሳቱን አጠፋለሁ ወንዙንም አደርቃለሁ የሚል
ተስፋ አልገባልንም፡፡ እሳቱ
እየነደደ ሳትቃጠሉ፣ ወንዙም ሞልቶ
እየፈሰሰ እናንተ ግን ሳትሰጥሙ እንዲታልፉ
አድርጋችኋለሁ ነው ያለን እንጂ፡፡ በዚህ
ሁኔታ ስንሆን አምላካችን ከሚነደው
የእቶን የበላይ ፣ የወንዙም ሙላት በእርሱ
ፊት ኃይል የሌለው መሆኑን እንማርበታለን፡፡
እሳቱ ቢጠፋና ውሃውም
ቢደርቅ የእግዚአብሔርን ታላቅነት የምናይበት
መንገድ ብዙም አይሆንም፡፡ ያስፈራንም የእሳቱ
መንደድና የወንዙ ሙላት
ነው፡፡ ያ ባይሆንማ ምኑን አይተን ነው
የምንፈራው፡፡ የሕይወት ጉዞ ያለ ምንም
መውጣትና መውረድ የምንጓዝበት ቢሆንማ
አትፍሩ ባልተባልን ነበር፡፡ የእግዚአብሐየርን
ሥራ በሰዎችም ሕይወት ያደረገውን ሁሉ በምናይበት
ጊዜ የሚያሰፈራውን
ነገር አጥፍቶና ግድሎ ሳይሆን ያ አስፈሪ
እንዳለ ሕዝቡን ግን ያስመለጠበትን ታሪክ
እንመለከታለን፡፡ የእሥራኤል
ሕዝብ ከግብዕ ባሪበት ወጥና አምልጦ ወደ
ተስፋው ምድር በሚጓዝበት ወቅት በፊታቸው
የነበረውን የኤሪትራን
ባሕር አላደረቀላቸውም ይልቁን ከፈለላቸውም
እንጂ፡፡ ሲድራቅ ፣ ምሳቅ አብዲናጎ
ወደ ሚነደው እቶን እሳት ውስጥ
በተጣሉ ጊዜ እሳቱን አላጠፋላቸውም ፣ ነገር
ግን ሰውነታቸውን የእሳቱ ሽታ እንኳ እንዳይነካቸው
ከሥስቱ ጋር አራተኛ
ሆኖ ወደ እሳቱ ገባ እንጂ፡፡ ዳንኤል ወደ
አንዳሳዎች ጉድ ጓድ የተጣለትን አስደናቂ
ታሪክ ስናይ ጌታ እነዚያን ጨካኝ
አናብስትን አልገደላቸውም፡፣ መላእክቱን
ልኮ አፋቸውን ዘግቶ ባሪያውን ግን በጭናቸው
እንተራሶ አሳደረው እንጂ፡፡
እነዚህን ታሪኮች ያየ ሁሉ የሚደደነቀው
ለዚህ ነው፡፡ ዛሬም ቢሆን እግዚአብሔር እሳት
ሲነድ ፣ ማዕበል ሲያናውጠን
፣ እዲሁም ደግሞ በመንገዳችን ወንዙ ሲሞላ
ሁሉ በዚያ ውስጥ ሰላም ያሳፈናል፡፡ ስለዚህ
እሳቱ እየነደደ፣ ሰይጣንም
እንደተራበ አንበሳ እያገሳ እኛ ግን በድል
እንጓዛለን፡፡ እግዚእሔርም ለእኛ ወዳዘጋጀልን
የክብር ሥፍራም እንደርሳለን
እንጂ በመንገድ አንቀርም፡፡ ስለዚህ ጌታ
አትፍሩ ይለናል፡፡
4.
በውሃ
ውስጥ የምናልፍበት ምክንያት እግዚአብሔር
በዚያ ውስጥ መንገድ ስላለው ነው(
ኢሳ.
43፡15)፡፡
እግዚአብሔር በዚያ መንገድ
ባይኖረው ኖሮ እኛም ባላለፍንና በዚያው ሰምጠን
በቀረን ነበር፡፡ ብዙ የምናውቃቸው ነገሮች
ቢኖሩንም የእግዚአብሔርን
መንገድ ማወቅ ግን እጅግ በጣም ከባድ ነው፡፡
የእግዚአብሔር መንገድ
እኛ ከለመድነው ውጭ ነው፡፡ እንደነ
ሙሴ የነበሩ የእግዚአብሔር ሰዎች የእግዚአብሐሔርን
መንገድ መወቅ እንዲችሉ አማላካቸውን
አጥብቀው
ለምነዋል፡፡
እርሱም ሲናገር መንገዱ ከእኛ መንገድ በፍጹም
የሚለይ መሆኑን ተናግሮናል፡፡ አሳባችሁ
እንደአሳቤ መንገዴም
እንደ መንገዳችሁ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፣
ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል እንዲሁ መንገዴ
ከመንገዳችሁ
አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው(
ኢሳ
55፡7)፡፡
እግዚአብሔር በወጀባና በአውሎ ነፋስ ውስጥ
መንገድ አለው(ናሆም
1፡7)፡፡
ስዚህም ይህ እግዚአብሔር
ሕዝቡን በራሱ
መንገድ እየመራ ምድረ በዳው ሳያቃጥለው፣
ውሃውም ሳያሰጥመው
ያሻግረዋል፡፡ ጎርፉ እንዳይወስደውም
ጥንቃቄ ያደርግለታል
ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የምንጓዝበት መንገድ
እግዚአብሔር
ያዘጋጀልን ስለመሆኑ እርግጠኛ እንሁን እንጂ
አውሎ ነፋስና ወጀብ ስለ መኖሩ አንጨነቅ፡፡
በምናነበው ክፍል
በቁ 16ላይ
የእግዚአብሔር
መንገድ እንዴት እንደሆነ
ሲናገር እግዚአብሔር በባሕር ውስጥ መንገድን
በኃይለኛም
ውሃ ውስጥ መተላለፊያን ያደርጋል
ይላል፡፡
5.
በእሳት
ውስጥ ስናልፍና
በውሃ ውስጥ ስንሄድ ጌታ ከእኛ ጋር
ይሆናል(ቁ.2፣5)፡፡
በውሃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፡፡
የእግዚአብሔር ነገር ፍፁም ለማመን የሚያስቸግር
አንዳንዴም ምኝነት ይመስላል፡፡ ይሁን አንጂ
ለሚታመኑበት
ደግሞ እውነት ነው፡፡ ከፍ ብሎ እንደተገለጸው
እሳት አያቃጥለንም ውሃም ሊያሰጥምን አይችልም
ስንል አንድ
ፍጥረታዊ ሰው ቢሰማን ስለ ሞኝነታችን ከልቡ
ሊስቅ ይችላል፡፡ ምስጥሩ ግን ውሃው የማስጠም
ባሕሪዩን ስለተው ወይም
እሳቱም ከማቃጠል በርዶ ሳይሆን ጌታ አብሮን
መኖሩ ልዩነቱን ማምጣቱ ነው፡፡ በሕይወታችን
እንደ እሳት የሚፈትን
ነገር ቢገጥመንና እንደ ማዕበልም ያለ ሁኔታ
ተነስቶ ቢያናውጠን ከሚናየው ነገር ይልቅ
ከእኛ ጋር ያለውን የጌታን
ህልውና እንመልከት፡፡
6. በእግዚአብሔር
ዓይን ታይተናል፣ በውድ ዋጋም ተገዝተናል(ቁ.1)፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን በእኛና
የእኛ በሆነው ሁሉ ላይ ባለቤት
ነው፡፡እርሱ በእኛና ጉዳዮቻችን ላይ ያገባዋል
፡፡ እሥራኤል እግዚአብሔርን ባለመታዘዛቸውና
በመንገዱ ባለመሄዳቸው
ምክንያት ጥቂት ጊዜ ቀጥቶአቸዋል፡፡ በዚህን
ጊዜ ምናልባት እግዚአብሔር ከምድር ላይ
የሚያጠፋቸው መስሎአቸው
አስበውም ይሆናል፡፡ ከዚህ የተነሳ በሕይወታቸው
ፈርተውና ሰግተው ሊሆን ይችላል፡፡ ግን እነርሱ
እንደሚያስቡት
ሳይሆን እግዚአብሔር ለእነርሱ የተለየ ልብ
ነበረው፡፡ ምንም እንኳን የማይታዘዙ ቢሆኑም
እግዚአብሔር አሁንም
ሕዝቡን ይፈልገዋል፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝቦች
በመሆናቸው ከእርሱም ጋር አብረው ስለኖሩ
እርሱ ዓመጽን እንደማይወድና
በዚያም ምክንያት እንደሚቀጣ ያውቃሉ፡፡
ለምርኮ የተጋለጡትም ካለመታዘዛቸው የነተነሳ
መሆኑን በደንብ
ተረድተዋል፡፡ ያ የእግዚአብሔር ቅጣት ያላላቀና
እነርሱም የሚጠፉ መስሎአቸው ፈርተዋል፡፡
ስለዚህ እግዚአብሔር
ነቢዩን ልኮ ሲያጽናናቸው “አሁንም
እሥራኤል ሆይ የፈጠረህም እሥራኤል ሆይ፣የ
ሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ
ይላል፡ ተበዥቼሃለሁና አትፍራ ፣ በስምህ
ጠርቼሃለሁና አንተ የእኔ ነህ” በማለት
ለሕዝቡ ያለው አቋም ያስረዳል፡፡ ስለ
ማነቱም ሲናገር እኔ አምላክህ ነኝ የሠራሁህም
እኔ ነኝ፣ ደግሞም በዋጋ ገዝቼህ ወደ እኔ
መልሼሃለሁ፡፡ ስለዚህ አንተ የእኔ
ስለሆንክ አትፍራ በማለት ያጽናናቸዋል፡፡
የአምልኩን ምሕረትና ቸርነት ለሚናፍቀው
የእሥራኤል ሕዝብ እግዚአብሔር
ያለው ጥንቃቄና ረህራሄ እጅግ በጣም ከፍ ያለ
መሆኑን ከዚህ አገላለጹ መረዳት እንችላለን፡፡
ምንም እንኳን እግዚአብሔርን
ማስደሰት የምንችልበት ማንነት ባይኖረንና
እርሱን የሚያሳዝን ነገሮችን ለማድረግ በጣም
የተጋለጥን ብንሆንም
አሁንም ስለ እኛ ግድ ይለዋል፡፡ እኛ የእግዚአብሔር
ነን፣ የእርሱ የእጅ ሥራዎች ነን ምክንያቱም
እርሱ ሠርቶናልና፡፡
እርሱ በዋጋ ገዝቶን የቃል ኪዳኑ ሕዝብ
አድርጎናል፡፡ ስለዚህ አትፍሩ ይለናል፡፡
No comments:
Post a Comment