የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ መንፈሳዊ ሕይወትን ያሳድጋል፣ የሚያስገኛቸውም ቁም ነገሮች ከቁጥር ያለፉ ናቸው። የዚያኑ ያክል ደግሞ ለመተርጐም የሚያስቸግሩ የምንባብ ክፍሎችና አረፍተ ነገሮችም አሉ። አስደንጋጭና ግራ መጋባት ውስጥ የሚከቱን መኖራቸውም ግልጽ ነው። ለምሳሌ ጌታ ሲናገር፦ “ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም” ያለው አሳብ አስደንጋጭ ነው። ጥያቄ ከሚፈጥሩብን መካከል “አስቆሮንቱ ይሁዳ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የሆነው እንዴት ነው?’ ኢየሱስ ደቀመዝሙሮችን ሲመርጣቸው ዲያብሎስ የሆነውን ይሁዳን ለምን አካተተው? (ዮሐ 6:70)። ለሚለው መልስ መፈለግ በራሱ ከባድ የቤት ሥራ ነው። ከደቀ መዝሙሮች መካከል “ዲያብሎስ” መሆኑ የተነገረለት ይሁዳ ነበር። አገልጋይ የሆነው በኢየሱስ ምርጫ ነው። ጌታም ማንነቱን እያወቀ መርጦታል ግን ለምን? ለመመለስ ያስቸግራል።
ይሁዳ ራሱ ወደ ኢየሱስ የቀረበ ለማስመስል ብዙ ተፍ ተፍ ይበል እንጂ የተለወጠ አገልጋይ አልነበረም። ከሌሎች ጋር ሐዋሪያ ተብሎ የወንጌል ምስክርነት ሲሰጥ ለካ እርሱ “ዲያብሎስ” ነበር። ጌታ ተአምራትን ሲያደርግ፣ በሁለት ዓሣና በአምስት እንጀራ በሺዎች የሚቆጠሩትን አጥግቦ አሥራ ሁለት መሶብ ሲስያተርፍ፣ ደቀመዛሙርትም ሰዎችን በሜዳው ላይ ባለው ሣር በሃምሳ ሃምሳ እያደረጉ አስቀምጠው ሲያገልግሉ አስቆሮቱ ይሁዳ አብሮአቸው ያገለግል ነበር። ይሁን እንጂ ሰውየው “ዲያብሎስ” ነበር። ዲያብሎስ መሆኑን ከኢየሱስና ከራሱ ከይሁዳ በቀር የሚያውቅ አልነበረም። እነዮሐንስ ያዕቆብና ጴጥሮስ ወዘተ ሌሎች ሐዋሪያት ይሁዳን በሐዋሪያነቱ እንጂ በዲያብሎስነቱ አላወቁትም። አብሮአቸው ብዙ ተጉዞአል፣ አገልግሏል፣ ምናልባትም አብሮአቸው ጸልዮም ይሆናል። እርሱ ግን ውጭው ሐዋሪያው ይሁዳ ውስጡ ግን አደገኛው ዲያብሎስ ሆኖ ኖሯል። እንደ ደቀመዛሙርት ቢያገለግልም ልቡን የገዛው ከጌታ ፍቅር ይልቅ የገንዘብ መጎምጀት ነው። ከኢየሱስ ይልቅ ገንዘብን አብልጦ በመውደዱ ለዲያብሎስ ቀኝ እጁ፣ የዓይኑም ብለን ሆኖ አገልግሏል። ኢየሱስን ለመሸጥ፣ ለጠላቶቹም አሳልፎ ለመስጠት ዋጋውን ሲተምን ሰንብቷል። ግን የሚባለው የኢየሱስ ደቀመዝሙር ነው። የተመረጠ ሐዋሪያ ነው። ፈረንጆች የመጽሐፉን ሽፋን አይተህ አትፍረድ የሚሉት ለዚህ አይደል?
ይህ አሳብ ሰው ስለ ደህንነቱ ቆም ብሎ እንዲያስብ የሚያደርግ ነው። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጅምላ ከማህበረ ምዕመናን ጋር የተቀላቀሉ ያልዳኑ ሰዎች ዛሬም ሊኖሩ እንደሚችሉ መጠርጠር ይኖርብናል ወይ ቢባል “በሚገባ እንጂ” የሚል ነው መልሱ። ያልዳነ ሐዋሪያ፣ ያልዳነ ወንጌላዊ፣ ያልዳነ ነቢይ ወይም መጋቢ ይኖራል ብሎ ማሰብ እንዴት ይቻላል? የሚሉ ብዙ ናቸው። ሰዎች የሚከራከሩት ስለ አገልጋይነት ጉዳይ ነው። አገልጋይ መሆን ለደህንነታችን ዋስትና አይሰጥም፣ ሊሰጥም አይችልም። አስተማሪ፣ ዘማሪ ፣ መስካሪ መሆን ዳግም መወለዳችንን አያረጋግጥም። ይህ አስደንጋጭና አስደማሚ ነው። ያለጥርጥር ለመቀበል የሚከብድ ነው። ግን ደግሞ የማይታበል ሐቅ የማይጠረጠር እውነታ ነው።
የይሁዳ ገርሞን ሳንጨርስ ኢየሱስ ጴጥሮስን “ሰይጣን” ማለቱ አያስደነግጥም? ጴጥሮስ በሐዋሪያት መካክል ዋናና አእማድ ተባለው ነበር። ሁሉን ትቶ ኢየሱስን የተከተለ ቆራጥና ተወዳጅ ሐዋሪያ! ለጌታ የሚቀናና ስለጌታ ሲል ራሱን ለሞት ለመስጠት የወሰነ ሐዋሪያ! ታዲያ አንድ ቀን ጌታ “ሰይጣን” ብሎ አረፈው። ታዲያ ማን ነው ሰው? ማነው አገልጋይ?
ይሁዳና ጴጥሮስ ሁለቱ የማይመሳሰል ማንነት አላቸው ። ይሁዳ ምኞቱና የልቡ ጩኼት ኢየሱስን ሽጦ ገንዘብ መቀበል ነበር። ጌታ እስክገልጠው ድረስ የዲያብሎስን አጀንዳ ለማስፈጸም የኖረ ነው። እንክርዳዱ ከስንዴው፣ እሾክም ከወይን ጋራ በአንድ ማሳ እንደሚኖሩ ከእውነተኞቹ ሐዋሪያት ጋር አብሮአቸው ኖሯል። ጴጥሮስ ሰይጣን የተባለበት ምክንያት ለኢየሱስ ያለውን ፍቅር በቃላት ለመግለጽ በሞከረበት ወቅት የተከሰተ ጉዳይ ነው። “ እርሱ ግን ዞር ብሎ ጴጥሮስን ፣ ወድ ኋላዬ ሂድ ፣ አንተ ሰይጣን የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና እንቅፋት ሆነህብኛል አለው(ማቴ 16:23)። ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ከሽማግሌዎችና ከካህናት አለቆች እንዲሁም ከጸሐፍት ብዙ መከራ እንደሚደርስበት፣ እንደሚገድልና እንዲሁም በሦስተኛ ቀን እንደሚነሳ ይገልጥ ዘንድ ሲጅምር ጴጥሮስ “ጌታ ሆይ አይሁንብህ ፣ ይህ አይድረስብህ ብሎ ኢየሱስን ገሰጸው። ይህንን ያለው ኢየሱስን ከማፍቀሩ የተነሳ ነበር። ቅንነቱንና ለጌታ ያለውን ፍቅር የገለጠበት መንገድ ይህ ቢሆንም አሳቡ ለካ ከእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድ ጋር ይጣረስ ኖሯል። ብዙዎቻችን እንደምናምነው ሰይጣን የጴጥሮስን ቅናአትና ለጌታም ያለው የሚቀጣጠል ፍቅር ለራሱ ዓላማ ተጠቅሞ በኢየሱስ በኩል ዓለምን ሁሉ ለማዳን የተዘረጋውን የእግዚአብሔርን ዕቅድ ለማሰናከል በጴጥሮስ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ሞከረ። ጌታ የገሰጸው ያንን የሰይጣንን ዓላማ ነው። እውነተኞችም አገልጋዮች ጸጋቸውንና መንፈሳዊ ቅንአታቸውን በእውቀትና በብስለት እንዲሆም በጥበብና በማስተዋል ካላላደረጉት መንፈሳዊ በሚመስሉ ሁኔታዎች በኩል ሰይጣን ጫና ሊፈጥርባቸው እንደሚችል ከዚህ እንማራለን።
ይሁዳ ዲያብሎስ የገባበት፣ የሰለጠነበት ልቡንም ለመንግሥቱ ያስወረሰ የዲያብሎስ መኖሪያ ለመሆን ራሱን የሰጠ possessed ሲሆን (ሉቃስ 22:3፣ዮሓ 13:27) ጴጥሮስ ግን ሰይጣን ተጽዕኖ ሊያሳድር ሙከራ ደረገበት Influenced አገልጋይ ነበረ። አማኞች ከሁለቱም የሰይጣን ተንኮሎች ራሳችንን መጠብቅ ይኖርብናል። እንደ ይሁዳ በአገልጋይነት፣ በነቢይነት፣ በሐዋሪያነት፣ በመጋቢነት፣ በወንጌላዊነት ወዘተ ስም ሕዝብን እያተራመሱ የእግዚአብሄርን ክቡር ዓላማ የሚያበላሹ ራሳቸውን ስለሚያውቁ ፈጥነው መመለስ ካልቻሉ የሰበሰቡትን ሳይበሉ ገመድ ያንቃቸዋል። እንደ ጴጥሮስም በመንፈሳዊ ቋንቋ የተለወሰውን የሰይጣንን ምክር እየሰሙ ከጠራቸው ጌታ ጋር የሚጣሉ ወደ ቃሉ መመለስ ያስፈልጋቸዋል። መልካም የሚመስሉን ልምምዶችና በውስጣችን የሚሰሙን ስሜቶች ሁሉ በሕያው የእግዚአብሔር ቃል እውነት ከልታሹና ካልተገሩ አደገኛነታቸው ከፍ ያለ መሆኑን ልብ ይሏል። ይሁዳ በመታነቅ ሕይወቱ ተደመደመች፣ እርሱም ወደ መረጣት የገዛ ራሱ ሥፍራ ሄደ(ሐዋ 1:25)። ጌታ ግን ጴጥሮስን በመገሰጽ ሕይወቱን አዳነው። መንፈስ ቅዱስም ሲሞላው ስለ ጌታው ትንሣኤ በድፍረት በመስበክ በሺዎች የሚቆጠሩትን ወደ እግዚአብሔር መንግስት ማረከ። ሰለ ኢየሱስ ሲል እጁን ለሰንሰለት ሰጠ። ከብዙ ተግባራትም መካከል ዘመን ተሻጋሪ ቃል ከጌታ ተቀብሎ ሁለት መጸህፍትን ጽፎ በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ ከተተው። ባለማወቅ ያደረገው ሳይታሰብ የጌታን ማዳን ሰብኮና ጽፎ መለኮታዊ ሰነድ ትቶልን ሄደ። ፍጻሜአችን እንደ ይሁዳ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በመልካም ይሁንልን። አምንእ!
ይሁዳ ራሱ ወደ ኢየሱስ የቀረበ ለማስመስል ብዙ ተፍ ተፍ ይበል እንጂ የተለወጠ አገልጋይ አልነበረም። ከሌሎች ጋር ሐዋሪያ ተብሎ የወንጌል ምስክርነት ሲሰጥ ለካ እርሱ “ዲያብሎስ” ነበር። ጌታ ተአምራትን ሲያደርግ፣ በሁለት ዓሣና በአምስት እንጀራ በሺዎች የሚቆጠሩትን አጥግቦ አሥራ ሁለት መሶብ ሲስያተርፍ፣ ደቀመዛሙርትም ሰዎችን በሜዳው ላይ ባለው ሣር በሃምሳ ሃምሳ እያደረጉ አስቀምጠው ሲያገልግሉ አስቆሮቱ ይሁዳ አብሮአቸው ያገለግል ነበር። ይሁን እንጂ ሰውየው “ዲያብሎስ” ነበር። ዲያብሎስ መሆኑን ከኢየሱስና ከራሱ ከይሁዳ በቀር የሚያውቅ አልነበረም። እነዮሐንስ ያዕቆብና ጴጥሮስ ወዘተ ሌሎች ሐዋሪያት ይሁዳን በሐዋሪያነቱ እንጂ በዲያብሎስነቱ አላወቁትም። አብሮአቸው ብዙ ተጉዞአል፣ አገልግሏል፣ ምናልባትም አብሮአቸው ጸልዮም ይሆናል። እርሱ ግን ውጭው ሐዋሪያው ይሁዳ ውስጡ ግን አደገኛው ዲያብሎስ ሆኖ ኖሯል። እንደ ደቀመዛሙርት ቢያገለግልም ልቡን የገዛው ከጌታ ፍቅር ይልቅ የገንዘብ መጎምጀት ነው። ከኢየሱስ ይልቅ ገንዘብን አብልጦ በመውደዱ ለዲያብሎስ ቀኝ እጁ፣ የዓይኑም ብለን ሆኖ አገልግሏል። ኢየሱስን ለመሸጥ፣ ለጠላቶቹም አሳልፎ ለመስጠት ዋጋውን ሲተምን ሰንብቷል። ግን የሚባለው የኢየሱስ ደቀመዝሙር ነው። የተመረጠ ሐዋሪያ ነው። ፈረንጆች የመጽሐፉን ሽፋን አይተህ አትፍረድ የሚሉት ለዚህ አይደል?
ይህ አሳብ ሰው ስለ ደህንነቱ ቆም ብሎ እንዲያስብ የሚያደርግ ነው። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጅምላ ከማህበረ ምዕመናን ጋር የተቀላቀሉ ያልዳኑ ሰዎች ዛሬም ሊኖሩ እንደሚችሉ መጠርጠር ይኖርብናል ወይ ቢባል “በሚገባ እንጂ” የሚል ነው መልሱ። ያልዳነ ሐዋሪያ፣ ያልዳነ ወንጌላዊ፣ ያልዳነ ነቢይ ወይም መጋቢ ይኖራል ብሎ ማሰብ እንዴት ይቻላል? የሚሉ ብዙ ናቸው። ሰዎች የሚከራከሩት ስለ አገልጋይነት ጉዳይ ነው። አገልጋይ መሆን ለደህንነታችን ዋስትና አይሰጥም፣ ሊሰጥም አይችልም። አስተማሪ፣ ዘማሪ ፣ መስካሪ መሆን ዳግም መወለዳችንን አያረጋግጥም። ይህ አስደንጋጭና አስደማሚ ነው። ያለጥርጥር ለመቀበል የሚከብድ ነው። ግን ደግሞ የማይታበል ሐቅ የማይጠረጠር እውነታ ነው።
የይሁዳ ገርሞን ሳንጨርስ ኢየሱስ ጴጥሮስን “ሰይጣን” ማለቱ አያስደነግጥም? ጴጥሮስ በሐዋሪያት መካክል ዋናና አእማድ ተባለው ነበር። ሁሉን ትቶ ኢየሱስን የተከተለ ቆራጥና ተወዳጅ ሐዋሪያ! ለጌታ የሚቀናና ስለጌታ ሲል ራሱን ለሞት ለመስጠት የወሰነ ሐዋሪያ! ታዲያ አንድ ቀን ጌታ “ሰይጣን” ብሎ አረፈው። ታዲያ ማን ነው ሰው? ማነው አገልጋይ?
ይሁዳና ጴጥሮስ ሁለቱ የማይመሳሰል ማንነት አላቸው ። ይሁዳ ምኞቱና የልቡ ጩኼት ኢየሱስን ሽጦ ገንዘብ መቀበል ነበር። ጌታ እስክገልጠው ድረስ የዲያብሎስን አጀንዳ ለማስፈጸም የኖረ ነው። እንክርዳዱ ከስንዴው፣ እሾክም ከወይን ጋራ በአንድ ማሳ እንደሚኖሩ ከእውነተኞቹ ሐዋሪያት ጋር አብሮአቸው ኖሯል። ጴጥሮስ ሰይጣን የተባለበት ምክንያት ለኢየሱስ ያለውን ፍቅር በቃላት ለመግለጽ በሞከረበት ወቅት የተከሰተ ጉዳይ ነው። “ እርሱ ግን ዞር ብሎ ጴጥሮስን ፣ ወድ ኋላዬ ሂድ ፣ አንተ ሰይጣን የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና እንቅፋት ሆነህብኛል አለው(ማቴ 16:23)። ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ከሽማግሌዎችና ከካህናት አለቆች እንዲሁም ከጸሐፍት ብዙ መከራ እንደሚደርስበት፣ እንደሚገድልና እንዲሁም በሦስተኛ ቀን እንደሚነሳ ይገልጥ ዘንድ ሲጅምር ጴጥሮስ “ጌታ ሆይ አይሁንብህ ፣ ይህ አይድረስብህ ብሎ ኢየሱስን ገሰጸው። ይህንን ያለው ኢየሱስን ከማፍቀሩ የተነሳ ነበር። ቅንነቱንና ለጌታ ያለውን ፍቅር የገለጠበት መንገድ ይህ ቢሆንም አሳቡ ለካ ከእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድ ጋር ይጣረስ ኖሯል። ብዙዎቻችን እንደምናምነው ሰይጣን የጴጥሮስን ቅናአትና ለጌታም ያለው የሚቀጣጠል ፍቅር ለራሱ ዓላማ ተጠቅሞ በኢየሱስ በኩል ዓለምን ሁሉ ለማዳን የተዘረጋውን የእግዚአብሔርን ዕቅድ ለማሰናከል በጴጥሮስ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ሞከረ። ጌታ የገሰጸው ያንን የሰይጣንን ዓላማ ነው። እውነተኞችም አገልጋዮች ጸጋቸውንና መንፈሳዊ ቅንአታቸውን በእውቀትና በብስለት እንዲሆም በጥበብና በማስተዋል ካላላደረጉት መንፈሳዊ በሚመስሉ ሁኔታዎች በኩል ሰይጣን ጫና ሊፈጥርባቸው እንደሚችል ከዚህ እንማራለን።
ይሁዳ ዲያብሎስ የገባበት፣ የሰለጠነበት ልቡንም ለመንግሥቱ ያስወረሰ የዲያብሎስ መኖሪያ ለመሆን ራሱን የሰጠ possessed ሲሆን (ሉቃስ 22:3፣ዮሓ 13:27) ጴጥሮስ ግን ሰይጣን ተጽዕኖ ሊያሳድር ሙከራ ደረገበት Influenced አገልጋይ ነበረ። አማኞች ከሁለቱም የሰይጣን ተንኮሎች ራሳችንን መጠብቅ ይኖርብናል። እንደ ይሁዳ በአገልጋይነት፣ በነቢይነት፣ በሐዋሪያነት፣ በመጋቢነት፣ በወንጌላዊነት ወዘተ ስም ሕዝብን እያተራመሱ የእግዚአብሄርን ክቡር ዓላማ የሚያበላሹ ራሳቸውን ስለሚያውቁ ፈጥነው መመለስ ካልቻሉ የሰበሰቡትን ሳይበሉ ገመድ ያንቃቸዋል። እንደ ጴጥሮስም በመንፈሳዊ ቋንቋ የተለወሰውን የሰይጣንን ምክር እየሰሙ ከጠራቸው ጌታ ጋር የሚጣሉ ወደ ቃሉ መመለስ ያስፈልጋቸዋል። መልካም የሚመስሉን ልምምዶችና በውስጣችን የሚሰሙን ስሜቶች ሁሉ በሕያው የእግዚአብሔር ቃል እውነት ከልታሹና ካልተገሩ አደገኛነታቸው ከፍ ያለ መሆኑን ልብ ይሏል። ይሁዳ በመታነቅ ሕይወቱ ተደመደመች፣ እርሱም ወደ መረጣት የገዛ ራሱ ሥፍራ ሄደ(ሐዋ 1:25)። ጌታ ግን ጴጥሮስን በመገሰጽ ሕይወቱን አዳነው። መንፈስ ቅዱስም ሲሞላው ስለ ጌታው ትንሣኤ በድፍረት በመስበክ በሺዎች የሚቆጠሩትን ወደ እግዚአብሔር መንግስት ማረከ። ሰለ ኢየሱስ ሲል እጁን ለሰንሰለት ሰጠ። ከብዙ ተግባራትም መካከል ዘመን ተሻጋሪ ቃል ከጌታ ተቀብሎ ሁለት መጸህፍትን ጽፎ በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ ከተተው። ባለማወቅ ያደረገው ሳይታሰብ የጌታን ማዳን ሰብኮና ጽፎ መለኮታዊ ሰነድ ትቶልን ሄደ። ፍጻሜአችን እንደ ይሁዳ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በመልካም ይሁንልን። አምንእ!
No comments:
Post a Comment